የምግብ እጥረት ጠቋሚ በኢትዮጵያ ይፋ ይተደረገው ‹‹ግጭት ባለባቸው ቦታዎች የምግብ አቅርቦትን ለማሻሻል በአጋርነት መሥራት›› በሚል መሪ ቃል ነው፡፡
የምግብ እጥት ብዙ ችግሮችን የሚያካትት በመሆኑ በትኩረት መሰራት እንዳለበት የጠቆሙት የጤና ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴኤታ ዶ/ር ደረጀ ዱጉማ፤ በ2021 የነበረውን ሂደት በሚያስረዳው ሪፖርት የመክፈቻ ዝግጅት ላይ ባደረጉት ንግግር እንደተናገሩት የኢትዮጵያ መንግስት የምግብና ስነ-ምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ የተለያዩ ፖሊሲዎችንና ስትራቴጂዎችን በመተግበር ላይ ይገኛል።
የጤና ሚኒስትር ዶ/ር ሊያ ታደሰ የኮቪድ-19 ወረርሽኝ ለመከላከልና ለመቆጣጠር ተሻሽሎ የወጣው መመሪያ ቁጥር 882/2014 በተመለከተ ጋዜጣዊ መግለጫ ሰተዋል፡፡
ባለፉት ሁለት አመታት በሃገራችን ኢትዮጵያ ወረርሽኙን ለመቆጣጠር እና ለመግታት የተለያዩ መመሪያዎችንና ደንቦችን በማውጣት ተግባራዊ ሲደረግ ቆይቷል፡፡
በጋራ የውይይት መድረኩ መክፈቻ ንግግር ያደረጉት የጤና ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴኤታ ዶ/ር ደረጀ ዱጉማ እንደተናገሩት የጤናው ዘርፍ ከፍተኛ አመራሮች የጋራ መድረኩ በዘርፉ የተከናወኑ ዋና ዋና ተግባራት አፈጻጸምን፣ ተግዳሮቶችን እና የተገኙ ልምዶችን በጋራ ለመገምገምና የቀጣይ አቅጣጫ ላይ ለመግባባት ይረዳል፡፡
የተለያየ ግጭት ያለባቸውን ሁሉንም አካባቢዎች በአግባቡ በመዳሰስ እና ሁሉም የኅብረተሰብ ክፍል አስፈላጊውን ድጋፍ እንዲያገኙ፣ በሆስፒታሎች እና በጤና ተቋማት አስፈላጊ ግብዓቶችን በማሟላት የተቋረጡ የሕክምና አገልግሎቶች መልሰው እንዲጀምሩ ማድረግ እንደሚገባ የገለፁት ዶ/ር ደረጀ ዱጉማ ይህም በጋራ የውይይት መድረኩ በትኩረት የሚገመገም አጀንዳ አንዱ መሆኑን አስረድተዋል፡፡
6.5 ሚሊዮን ብር የሚያወጣ የላብራቶሪ ህክምና ቁሳቁስ ድጋፍን ያደረገው የኦሃዮ ስቴት ግሎባል ዋን ሄልዝ ሲሆን በጦርነት ጉዳት የደረሰባቸው የህክምና ተቋማትን መልሶ ለማቋቋም የሚውል መሆኑ ተገልጿል፡፡
የጤናው ዘርፍ በጦርነቱ ከፍተኛ ውድመት ያሰተናገደ ዘርፍ መሆኑን የገለጹት የጤና ሚኒስቴር ሚንስትር ዴዔታ ዶ/ር አየለ ተሸመ፤ የተደረገው ድጋፍ ያጋጠሙትን ችግሮች ለመቅረፍ የሚረዳ መሆኑን ገልጸዋል፡፡
የላብራቶሪ ህክምና ቁሳቁስ ድጋፍ የተደረገላቸው ተቋማት የተሟላ የህክምና አገልግሎት ለመስጠት እንዲችሉ እየተደረገ ያለውን ጥረት የሚደገፍ መሆኑን በመግለጽ ስለተደረገው ድጋፍ በጤና ሚኒስቴር፣ ድጋፍ በተደረገላቸው ተቋማት እና በተቋማቱ አገልግሎት በሚያገኙ ማህበረሰቦች ስም ምስጋና አቅርበዋል፡፡
16ኛው አመታዊ የቲቢ ምርምር ጉባኤ ላይ ከተገኙ የአጎራባች ሃገራት ተወካዮችጋር የቲቢ በሽታን መከላከልና መቆጣጠር በተመለከተ የጎንዮሽ ውይይት ተካሂዷል።
አጎራባች ሀገራት በሚዋሰኑባቸው አከባቢዎች ተመሳሳይ ማህበረሰብ የሚገኝባቸው በመሆናቸው እና በተለይም አርብቶ አደር በሚበዛባቸው የምስራቅ አፍሪካ አጎራባች አከባቢዎች የቲቢ በሽታ ህክምናን ለመስጠትም ሆነ ክትትል ለማድረግ አዳጋች በመሆኑ ሃገራቱ በጋራ መስራታቸው ጠቀሜታው የጎላ ይሆናል።
በአጎራባች አከባቢዎች ያለው ነባራዊ ሁኔታን የሚያመለክት በቂ መረጃ አለመኖር እና የግብአት ውስንነት ማነቆ መሆኑን ተወካዮች አውስተው የምርምር ተግባራትን በስፋት መስራት፣ ትብብርን ማጠናከርና ለጉዳዩ ትኩረት እንዲሰጥ ከፍተኛ ሃላፊዎችን ማስገንዘብና የሚድያና ተግባቦት ፕላትፎርም ተፈጥሮ በትኩረት በጋራ መስራት አስፈላጊ እንደሆነ ጠቁመዋል።
አመታዊ ብሔራዊ የቲቢ ምርምር ጉባኤ በዚህ አስቸጋሪ ወቅት መደረጉ ጠቀሜታው የጎላ ነው ያሉት የጤና ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴኤታ ዶ/ር አየለ ተሾመ አገራች ኢትዮጵያ በተከሰተው ጦርነት እና የተለያዩ ግጭቶች ምክንያት በጤና ተቋማት ላይ የደረሰው ውድመቶች እና የጤና ተቋማት መስተጓጎል፤ የህዝብ መፈናቀል፤ የድርቅ መስፋፋት እና በኮቪድ 19 ወረርሽኝ ምክንያቶች በቲቢ በሽታ መከላከል እና ቁጥጥር ላይ የተመዘገቡ ስኬቶች እንዳይቀለበሱ በቁርጠኝነት ልንሰራ ይገባል ብለዋል፡፡
በየአመቱ በሚካሄደው የቲቢ ምርምር ጉባኤ ላይ የሚቀርቡ የምርምር ሥራዎች የቲቢ በሽታን በመከላከልና በመቆጣጠር ረገድ ከፍተኛ አስተዋፅኦ እያደረገ እንደሆነ ተናግረዋል፡፡
አገራች ኢትዮጵያ የቲቢ በሽታ ስርጭት ለመግታትና ቲቢ ለማጥፋት ዘመናዊ የምርመራ መሳሪያዎችን በጤና ተቋማት በማስገባት አገልግሎቱ ተደራሽ በማድረግና በየአምስት አመቱ የሚተገበር እቅድ በማዘጋጀት እየተሰራ ነው ተብሏል፡፡
በሃገራችን በተካሄደው በህግ ማስከበር እና በህልውና ዘመቻው ላይ አስተዋጽኦ ላበረከቱ ጤና ተቋማት፣ ጤና ክብካቤ ባለሙያዎችና የተለያዩ ባለድርሻ አካላት በኢ.ፌ.ዲ.ሪ ጤና ሚኒስቴር እና በኢ.ፌ.ዲ.ሪ መከላከያ ሚኒስቴር በጋራ የተዘጋጀ የምስጋና የእውቅና መርሃ ግብር ተካሄደ፡፡
በፕሮግራሙ ላይ በክብር እንግድነት የተገኙት ጠቅላይ ሚኒስትር ክቡር ዶ/ር አብይ አህመድ ባደረጉት ንግግር የጤና ባለሙያዎችና የጤና ክብካቤ ሰራተኞች እንደ ሰው፣ እንደ ኢትዮጵያዊ እና እንደ ሃኪም ሶስት ማንነትን ተላብሳችሁ ለሰራችሁት ታላቅ ገድል ከፍተኛ ምስጋና ይገባችኋል ብለዋል፡፡
ድጋፉን ያደረገው የኮካ ኮላ ኩባንያ የአለም በጎ አድራጎት ክንፍ የሆነው ኮካ ኮላ ፋውንዴሽን ነው፡፡
በቅዱስ ጳውሎስ ሆስፒታል ይፋዊ የርክክብ ስነ-ስርአቱ ላይ በክብር እንግድነት የተገኙት የጤና ሚኒስቴር ሚኒስትር ዶ/ር ሊያ ታደሰ የተደረገው ድጋፍ የቅዱስ ጳውሎስ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ለታካሚዎች የጤና አገልግሎት ለመስጠት ያለውን አቅም ለማሳደግ ትልቅ አስተዋጽኦ ይኖረዋል ብለዋል፡፡
የጤና ሚኒስቴር፣ የግብርና ሚኒስቴር፣ የትምህርት ሚኒስቴር እና አጋር አካላት በኢትዮጵያ ህብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት አስተባባሪነት በጋራ ያዘጋጁት በኢትዮጵያ የመጀመሪያ የሆነውን ምግብን መሠረት ያደረገ የአመጋገብ መመሪያ (Food-Based Dietary Guidelines (FBDG's) በዛሬው ዕለት ይፋ ሆኗል።