Articles

የዲጂታል ጤና ዘርፍ መሪ (Champion) በመሆን የተሰጣቸዉን ኃላፊነት አስመልክቶ የአፍሪካ በሽታ መቆጣጠሪያ እና መከላከያ ማዕከል (Africa CDC) ዋና ዳይሬክተር ከሆኑት ከዶክተር ዣን ካሴያ ጋር ዉጤታማ  ውይይት አድርገዋል 

AI

በውይይታቸዉም በተለያዩ ቅድሚያ የሚሰጣቸው ጉዳዮች ላይ የመከሩ ሲሆን፤ በተለይም በአፍሪካ ሕብረት የሰው ሰራሽ አስተውሎት (AI) እና የዲጂታል ጤና ዘርፍ መሪ (Champion) በመሆን የተሰጣቸዉን አዲስ ኃላፊነት በሚመለከት በስፋት ተነጋግረዋል።


የፈጠራ ሥራዎች ለአፍሪካ ዕድገት ምንጊዜም ወሳኝ መሰረት ናቸዉ ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐብይ አህመድ በጤናው ዘርፍ የሚገጥመንን ተለዋዋጭ ተግዳሮቶች ለመወጣት የሰው ሰራሽ አስተውሎትንና የዲጂታል ቴክኖሎጂዎችን ዐቅም መጠቀም የጤና ሥርዓታችንን ለማጠናከር፣ ተደራሽነትን ለማስፋፋት እና ለሕዝባችን የተሻለ ውጤት ለማስመዝገብ ወሳኝ ነው ብለዋል። 

የአውሮፓ - የአፍሪካ ህብረት ለአፍሪካ ጤና አጋርነት ከ100 ሚሊዮን ዩሮ በላይ የድጋፍ ፓኬጆች ይፋ ሆኑ

EU-African Union

የአፍሪካን የጤና ደኅንነት፣ ጽናትና ሉዓላዊነት በማጠናከር ረገድ ትልቅ ምዕራፍ የሆነውን የአፍሪካ-አውሮፓ ህብረት የጤና አጋርነት የድጋፍ ፓኬጆች በሶስት አዳዲስ ኢኒሼቲቮች ላይ ትኩረት ያደረገ ነው ተብሏል።

ጠንካራ ስርዓት፣ ጠንካራ ተቋማት እና ለማህበረሰቡ የተሻሉ የጤና ውጤቶች እንዲመጡ ከአፍሪካ ሲዲሲ፣ ከአውሮፓ ህብረት እና ከሁሉም አጋሮች ጋር በቅርበት ለመስራት ኢትዮጵያ ሙሉ በሙሉ ቁርጠኛ ነች ብለዋል የጤና ሚኒስትር ዶ/ር መቅደስ ዳባ።

ሁለቱ አህጉራት የአፍሪካን የጤና ሉዓላዊነት እና ሰፊ የዘላቂ ልማት ግቦችን ለማሳካት ወቅታዊና የወደፊት የጤና ስጋቶችን ለመቅረፍ እየተደረገ ያለውን ጥረት በመቀጠል የአፍሪካ - የአውሮፓ ህብረት በአፍሪካ የበሽታ መቆጣጠሪያና መከላከያ ማእከል ሲዲሲ የረጅም ጊዜ እና አጠቃላይ የጤና አጋርነታቸውን አጠናክረው መቀጠላቸውን ጠቁመዋል።

በቅዱስ ጳውሎስ ሆስፒታል ሚሊኒየም ሜዲካል ኮሌጅ የአከርካሪ ቀዶ ህክምና ማዕከል /National spine center/ ስራ ጀመረ 

St. Paul

በቅዱስ ጳውሎስ ሆስፒታል ሚሊኒየም ሜዲካል ኮሌጅ ግቢ የተገነባዉ የአከርካሪ ቀዶ ህክምና ማዕከል /National spine center/ የጤና ሚኒስትር እና ሌሎች ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች ፣ በኢትዮጵያ የእስራኤል ም/አምባሳደር፣ የጄዲሲ መስራችና አንጋፋ የቀዶ ህክምና ባለሙያዎች የቅዱስ ጳውሎስ አመራሮች እንዲሁም በርካታ ባለድርሻ አካላት በተገኙበት ተመርቆ ስራ ጀምሯል።