የህዝብ ግንኙነት እና ኮሙዩኒኬሽን ዳይሬክቶሬት
የማንኛውም ተቋም የመንግስትም ይሁን የግል ስኬት በስሙ ላይ በእጅጉ የተመካ ነው። የተገልጋዮች፣ የሰራተኞች ፣ የባለሀብቶች ፣ የፖሊሲ አውጪዎች እና የመገናኛ ብዙኃን አስተያየቶች በአንድ ድርጅት ብልጽግና ላይ ኃይለኛ ተፅእኖ አላቸው። ስለ ተቋሙ ያላቸው ግንዛቤ ከተቋሙ ጋር መሥራትና መደገፍ ይፈልጉ እንደሆነ ውሳኔዎቻቸው ላይ ተፅዕኖ ያደርጋል። በዚህ ምክንያት የድርጅትን ስም ለመገንባት፣ ግንዛቤን እና ድጋፍን ለማግኘት እንዲሁም በሕዝብ አስተያየትና ባህሪ ላይ ተጽዕኖ ለማሳደር ጠንካራ የግንኙነት መስመር አስፈላጊነት የማይካድ ነው።