ኢትዮጵያ የአደጋ ጊዜ የሕክምና ቡድን (EMT) አቅሟን በማጠናከር ዓለም አቀፍ የጤና አጋርነቷን እያሰፋች ነው

ACHIEVE Africa

የጤና ሚኒስቴር ከጀርመን ኤምባሲ፣ ከሮበርት ኮች ኢንስቲትዩት እና ከዓለም የጤና ድርጅት (WHO) ጋር የአደጋ ጊዜ የሕክምና ቡድኖች ተነሳሽነት እና አጋርነት በተመለከተ  የውይይት መድረክ ተካሂዷል።

በመድረኩ የጀርመን አምባሳደር ብርጊት ኦሪ ኢትዮጵያ የመጀመሪያውን ዓለም አቀፍ የአደጋ ጊዜ የሕክምና ቡድኖች  ዓለም አቀፍ ስብሰባ እንደምታስተናግድ አስታውቀዋል፣ ይህም አገሪቱ የተጠናከረ የአደጋ ጊዜ ምላሽ አቅም መገንባቷን እና የማርበርግ ቫይረስን ጨምሮ የቅርብ ጊዜ ወረርሽኞችን ውጤታማ በሆነ መንገድ መከላከል መቻሏን ማሳያ መሆኑን አስረድተዋል።

በ39ኛው የአፍሪካ ህብረት መደበኛ ጉባኤ የሚኒስትሮች የጎንዮሽ ስብሰባ በኢትዮጵያ በህጻናት ጤና እና በምግብ ዋስትና ረገድ የተመዘገቡ ስኬቶችን ማሳየት ችላለች

12

በአፍሪካ የህፃናት ጤና እና ስርዓተ-ምግብ ላይ ያተኮረው መድረክ የአፍሪካ ህብረት የስርዓተ-ምግብ ሻምፒዮን የሆኑት የሌሶቶ ግርማዊ ንጉሥ ሌቲ ሳልሳዊ፣ ከከፍተኛ የመንግስት ባለስልጣናትና ከዓለም አቀፍ ተቋማት ተወካዮች ተሳትፈዋል።

በዝግጅቱ ላይ ንግግር ያደረጉት በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ማዕረግ የዲሞክራሲ ግንባታ ማስተባበሪያ ማዕከል ኃላፊ አቶ አደም ፋራህ፣ ኢትዮጵያ የሌማት ቱሩፋት እና  የአረንጓዴ ሌጋሲ አስርት ዓመታት ተነሳሽነቶችን በተሳካ ሁኔታ በመተግበር ጉልህ ውጤቶችን ማስመዝገባን ተናግረዋል።

እንደ አቶ አደም ገለጻ፣ ፕሮግራሞቹ በመላ አገሪቱ የሚገኙ በሚሊዮን የሚቆጠሩ እናቶችንና ህጻናትን የተመጣጣኝ ምግብ አቅርቦትን በማሻሻልና የመቋቋም አቅምን በማጠናከር ተጠቃሚ አድረገዋል።

መንግስት የተመጣጠነ እና ደህንነቱ የተጠበቀ የምግብ አቅርቦትን ለማረጋገጥ ያለውን ቁርጠኝነት አረጋግጠው፣ ቀጣይነት ያለው ጥረት የወደፊት ትውልድ ደህንነትን ለመጠበቅ እንደሚያስችል አፅንዖት ሰጥተዋል።

የአፍሪካን የክትባት እና የሕክምና ሉዓላዊነትን ለማረጋገጥ ያለመው ግዙፉ "ACHIEVE Africa" የተሰኘ ኢኒሼቲቭ ከ39ኛው የአፍሪካ ህብረት የመሪዎች ጉባኤ ጎን ለጎን በይፋ ተመሠርቷል 

Dr Mekdes Daba

​በኢኒሼቲቩ ማስጀመሪያ መርሃ-ግብር ላይ የተገኙት የጤና ሚኒስትር ዶ/ር መቅደስ ዳባ፤ ኢትዮጵያ የአፍሪካ ህብረት እ.ኤ.አ በ2040 የክትባት ፍላጎትን 60 በመቶ በአህጉር ውስጥ ለማሟላት ያስቀመጠውን ግብ ለማሳካት ግንባር ቀደም ሚና እየተጫወተች መሆኑን የገለጹ ሲሆን መንግስት የመድኃኒት ግዥ ስርዓቱን በአገር ውስጥ ለሚመረቱ ምርቶች ቅድሚያ እንዲሰጥ በማሻሻሉ፣ በዘርፉ የአገር ውስጥ ፍላጎትን ሽፋን ከ8 በመቶ ወደ 42 በመቶ ማደጉን ጠቁመው በቀጣይ አምስት ዓመታት ወደ 60 በመቶ ለማሳደግ ታቅዶ በትኩረት እየተሰራ መሆኑንም አረጋግጠዋል።
\
​ኢትዮጵያን የፈጠራ ማዕከል (Innovation Hub) ለማድረግ ሰፊ ስራዎች እየተሰሩ መሆኑን የገለጹት ዶ/ር መቅደስ የሀገሪቱ የክትባት የማምረት ጉዞ አሁን ላይ "ይሳካል ወይ?" የሚለው ጥያቄ ቀርቶ "እንዴት እና በምን ፍጥነት?" ወደሚለው ወሳኝ ምዕራፍ መሸጋገሩን አስታውሰዋል። 

ከመላው አፍሪካ የተውጣጡ የጤና ሚኒስትሮች እና ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች የአፍሪካ ህብረት የመሪዎች ጉባኤ የጎንዮሸ ስብሰባ መካሄድ ጀምሯል

Dr Mekdes Daba

"የአፍሪካን የጤና ደህንነት እና የሉዓላዊነት አጀንዳ ማራመድ፡ ቁርጠኛ ፋይናንስ እና አመራርን በመጠቀም ዘላቂነትን ማረጋገጥ" በሚል መሪ ቃል የአፍሪካን የጤና ስርዓቶች በዘላቂ ፋይናንስ፣ ጠንካራ አመራር እና በራስ መተማመንን ለማረጋገጥ በተሻለ አህጉራዊ ትብብርን ማጠናከር ላይ ያተኮረ የጎንዪሽ  ስብሰባ በአፍሪካ የበሽታ መቆጣጠሪያ እና መከላከያ ማዕከል( Africa CDC) እየተካሄደ ይገኛል። 

በስብሰባው ላይ የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የኢፌድሪ የጤና ሚኒስትር እና በአፍሪካ የበሽታ መቆጣጠሪያ እና መከላከያ ማዕከል( Africa CDC) የቦርድ ም/ሰብሳቢ ዶ/ር መቅደስ ዳባ ዝግጅቱን “የአመራር ቁርጠኝነት ማሳያ” ሲሉ ገልጸውታል። ስብሰባው በአፍሪካ አገሮች መካከል ያለውን የጤና ደህንነት እና ሉዓላዊነት ለማሳደግ ያለንን የጋራ ቁርጠኝነት የሚያንፀባርቅ መሆኑን ተናግረዋል። 

በኢትዮጵያ በስርዓተ-ምግብ ማሻሻያ እርምጃዎች በተሰራዉ ስራ ተምሳሌት የሚሆን ዉጤት ተገኝቷል - የሌሴቶ ንጉስ ግርማዊ ሌቲ ሳልሳዊ

nutrition

የሌሴቶ ንጉስ ግርማዊ ሌቲ ሳልሳዊ ከጤና ሚኒስትር ዶ/ር መቅደስ ዳባ ጋር በአዲስ አበባ በሚገኘው ዘውዲቱ መታሰቢያ ሆስፒታል የህፃናት እንክብካቤ እና የስርዓተ-ምግብ ክፍልን ጎብኝተዋል፣ በጉብኝታቸው ኢትዮጵያ የእናቶችን እና የህፃናትን ጤና ለማሻሻል ያላትን ቁርጠኝነት አድንቀዋል።

በጉብኝቱ ወቅት ንግግር ያደረጉት ግርማዊ ንጉስ ሌቲ “ውጤታማ የስርዓተ-ምግብ እርምጃ ህይወትን ያድናሉ” በማለት አፅንኦት ሰጥተው፤ በኢትዮጵያ  በስርዓተ-ምግብ ማሻሻያ እርምጃዎች በተሰራዉ ስራ ተምሳሌት የሚሆን ዉጤት ተገኝቷል ብለዋል። ስርዓተ-ምግብ በሽታን በመከላከል እና የህፃናትን ሞት በመቀነስ ረገድ ያለውን ወሳኝ ሚናም ገልጸዋል። 

ንጉሱ እንዳሉት ኢትዮጵያ እናቶችን እና ህፃናትን ለመጠበቅ የምታደርገውን ጠንካራ ጥረት በገዛ ዓይናቸው ለማየት መቻላቸውን ተናግረው፤ አገሪቱ ስርዓተ-ምግብን ከጤና አጠባበቅ አደረጃጀቷ ጋር በማዋሃድ ዘላቂ የጤና ውጤቶችን ለማሳካት የሚያስመሰግን እና ስትራቴጂካዊ አቀራረብ መከተሏን ገልጸዋል።

ኢትዮጵያ የማርበርግ ቫይረስ በሽታን በመቆጣጠር ረገድ ስኬታማ ሆናለች 

Dr Mekdes Daba

ኢትዮጵያ የማርበርግ ቫይረስን በመቆጣጠር ያደረገችው ስኬታማ ጥረት በጠንካራ አመራር፣ ፈጣን ምላሽ እና በተቀናጀ እርምጃ ትልቅ የህብረተሰብ ጤና ስኬትን ማስመዝገቧን የኤፌዴሪ የተወካዮች ምክር ቤት አፈጉባኤ የተከበሩ ታገሰ ጫፎ ገልፀው፤ ስኬቱ የጤና ፖሊሲ፣ የጤና ባለሙያዎች፣ እና ባለድርሻ አካላት የጋራ የመተባበር እና የመደመር ውጤት ነው ብለዋል።
 
የጤና ሚኒስትር ዶ/ር መቅደስ ዳባ  በሃገራችን የጤና ታሪክ ትልቅ የስኬት አሻራ የጣለ ተሞክሮ መሆኑን ገልፀው፤ ማህበረሰቡን በማስተባበር ፈጣን ምላሽ በመስጠት ቫይረሱ ሊያደርስ የሚችለውን ጉዳት መቀነስ መቻሉን ተናግረዋል።

በኢትዮጵያ በአዲስ ቴክኖሎጂ ህክምና የሚሰጥ የመጀመሪያው የስትሮክ ህክምና ማእከል በዛሬው እለት ተመርቆ ተከፍቷል።

stroke treatment center

የጤና ሚኒስትር ዶክተር ሊያ ታደሠ በምርቃት ስነስርዓቱ ላይ ተገኝተው ባደረጉት ንግግር እንዳሉት የጤናው ዘርፍ በርካታ መሻሻሎች እያሣየ ያለ ቢሆንም ገና ብዙ ወደ ፊት መሄድ ይጠበቅበታል ብለዋል። የአክሶል ስትሮክ እና ስፓይን ማእከል መከፈቱ እንደ ሀገር የእስትሮክ ህክምናን አንድ ምእራፍ ወደ ፊት የሚወስድ መሆኑን ጠቅሰው ማእከሉ  ለዚህ ምረቃ በመድረሱ ያላቸውን አድንናቆት ገልጸዋል። ይህ አዲስ ቴክኖሎጂ እና የተለየ አገልግሎት ይዞ የመጣ ማእከል በአገሪቱ መከፈት መቻሉ ለጤናው ዘርፍ ትልቅ አስተዋጽኦ እንደሚኖረውም ዶክተር ሊያ ተናግረዋል።


ላለፋት አመታት ተላላፊ ያልሆኑ በሽታዎች እና በዚህ ሳቢያ የሚመጣ ሞት እየጨመረ መምጣቱን የገለጹት ዶክተር ሊያ ይህን ችግር ለመቅረፍ የጤና ሚኒስቴር ከመከላከል ስራው ጎን ለጎን የስፔሻሊቲ ህክምና አገልገግሎት ማስፋፋት ስራ የሚያሰራ የአስር አመት ፍኖተ ካርታ  ተዘጋጅቶ እየተተገበረ መሆኑን አስረድተዋል።

የጡት ካንሰር ግንዛቤ ማስጨበጫ ንቅናቄ ተጀመረ

Breast cancer

በዓለም አቀፍ ደረጃ በየዓመቱ በፈረንጆች ጥቅምት ወር የሚደረገው የጡት ካንሰር ግንዛቤ ማስጨበጫ ንቅናቄ በፓዮኒር ምርመራ ማዕከል ከመስከረም 20 ጀምሮ ለአንድ ወር በነፃና በግማሽ ክፍያ በሚሰጥ ምርመራ ተጀምሯል።


በየዓመቱ 40 ሺህ ያህል ሰዎች በጡት ካንሰር ምክንያት እንደሚሞቱ የጠቆሙት በጤና ሚኒስቴር የእናቶችና ሕፃናት ጤና ዳይሬክተር ዶክተር መሠረት ዘላለም ካንሰር ስር ከሰደደ በኋላ ለማከም የሚያደርሰውን የጤና፣ ማህበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ ጫና ለመቀነስና ለመከላከል ቀድሞ በመመርመር የጤናን ሁኔታ ማወቅ እንደሚገባ አሳስበዋል።

በጤና ሚኒስትር ዴኤታ ክቡር ዶ/ር ደረጀ ዱጉማ የተመራ የኢትዮጵያ ልዑካን ቡድን በቪየና ኦስትሪያ በተካሄደዉ 66ኛው የIAEA ጠቅላላ ጉባኤ ላይ ተሳትፈዋል፡፡

Ethiopian delegation

"በኑክሌር መስክ ዓለም አቀፍ ትብብር!" በሚል መሪ ቃል  በቪየና ኦስትሪያ በተካሄደዉ 66ኛው የIAEA ጠቅላላ ጉባኤ ላይ በጤና ሚኒስትር ዴኤታ ክቡር ዶ/ር ደረጀ ዱጉማ የተመራ የኢትዮጵያ ልዑካን ቡድን ተሳትፈዋል፡፡


በኤጀንሲው ዋና መስሪያ ቤት በቪየና ኢንተርናሽናል ሴንተር (VIC) በቪየና ኦስትሪያ የተካሄደዉ ይህ ጉባኤ ከኒዩክሌር ቴክኖሎጂ እና ሳይንስ ዙሪያ ለህክምና አገልግሎት ጥቅም የሚዉሉ ቴክኖሎጂዎችን በተለይም የካንሰር ጨረር ህክምናን ጨምሮ ለተለያዩ ህክምና ዘርፎች ጥቅም ላይ በሚዉሉ የኑክሌር ቴክኖሎጂ እና ሳይንስ ርዕሰ ጉዳዮች ላይ መክረዋል፡፡

   
በ66ኛው የIAEA ጠቅላላ ጉባኤ የኢትዮጵያ ተወካዮች ከአክሽን ፎር ካንሰር ቴራፒ (PACT) መርሃ ግብሮች ቡድን ጋር በቀጥታ ውይይት በማድረግ በኢትዮጵያ እና በIAEA መካከል ስላለው እና የወደፊት የቴክኒክ ትብብር በተመለከተም ተወያይተዋል።