የጤና አገልግሎት ጥራት ዳይሬክቶሬት
ራዕይ
ጤናማ ፣ አምራች እና የበለፀገ ማህበረሰብ ማየት
ተልዕኮ
ስልታዊ ዕቅድ በማቀድ እንዲሁም ጥራት ያለው የጤና አገልግሎት አሰጣጥን በማሻሻል እና በመቆጣጠር የኢትዮጵያውያንን ጤና እና ደህንነት ማሳደግ
ጤናማ ፣ አምራች እና የበለፀገ ማህበረሰብ ማየት
ስልታዊ ዕቅድ በማቀድ እንዲሁም ጥራት ያለው የጤና አገልግሎት አሰጣጥን በማሻሻል እና በመቆጣጠር የኢትዮጵያውያንን ጤና እና ደህንነት ማሳደግ
የዚህ ፕሮግራም ዓላማ ነባር የጤና ተቋማትን መልሶ በማቋቋምና አዳዲስ መገልገያዎችን በመገንባት የጤና አገልግሎቶች ተደራሽነትን ማሳደግ እና ጥራትን ማሻሻል ነው። ዓላማው በቂ የህክምና መሳሪያዎች፣ ሠራተኞችና አስተዳደር ያላቸው የጤና ተቋማት፣ ለደንበኛ ተስማሚና ደረጃውን የጠበቀ የጤና ተቋም አቀማመጥ፣ ዘላቂ ተቋምና የመሣሪያ ጥገና እና በመጨረሻም በአይቲ የተደገፈ የጤና ስርዓት ለማቅረብ ነው።
በፌዴራል ጤና ጥበቃ ሚኒስቴር በፕሮግራሙ ክንፍ ስር ከሚገኙት ዳይሬክቶሬቶች መካከል የጤና ኤክስቴንሽን ፕሮግራም እና የመጀመሪያ ደረጃ ጤና እንክብካቤ ዳይሬክቶሬት አንዱ ነው። የዳይሬክቶሬቱ ዋና ሚናዎች እና ኃላፊነቶች አስፈላጊ መመሪያዎችን እና ስትራቴጂዎችን በማዘጋጀት እንዲሁም ለሁሉም የኢትዮጵያ ክልሎች አስፈላጊውን ድጋፍ በመስጠት የመጀመሪያ ደረጃ የጤና እንክብካቤ እንቅስቃሴዎችን በመደገፍ እና በመከታተል ሁለንተናዊ የጤና ሽፋን ዕውን ማድረግ ነው።
ዳይሬክቶሬቱ በሰሩ 3 የጉዳይ ቡድኖች አሉት፤ እነሱም የጤና ኤክስቴንሽን ፕሮግራም እና የመጀመሪያ ደረጃ የጤና እንክብካቤ ጉዳይ ቡድን ፣ የጤና ትምህርት እና ማስተዋወቂያ ጉዳይ ቡድን እንዲሁም የጤና ማዕከል ተሃድሶ ጉዳይ ቡድን ናቸው። የእያንዳንዱ ጉዳይ ቡድን ሚናዎች እና ኃላፊነቶች እንዲሁም ፕሮግራሞች፣ ፕሮጄክቶችና ተነሳሽነቶች ከዚህ በታች ተብራርተዋል።
የሚኒስትሮች ምክር ቤት በኢ.ፌ.ዲ.ሪ የአስፈፃሚ አካላት የሥልጣን እና ግዴታ ፍቺዎች መሠረት ደንብ ቁጥር 144/2007 አውጥቷል።
ከመንግስትም ሆነ ከልማት አጋሮች የተገኙ የገንዘብ ሀብቶች ተገቢ አጠቃቀምን ማረጋገጥ!
የፋይናንስና ግዥ ዳይሬክቶሬት ዓላማ ከመንግስትም ሆነ ከልማት አጋሮች የተገኙ የፋይናንስ ሀብቶች ተገቢ አጠቃቀምን ከማረጋገጥ በተጨማሪ የሚኒስቴሩ የገንዘብ ገቢና ወጪዎች በሀገሪቱ የፋይናንስ ሕጎችና መመሪያዎች መሠረት መከናወናቸውን እንዲሁም የጤና ልማት አጋሮች መስፈርቶችን ማክበራቸውን ማረጋገጥ ነው። በተጨማሪም የእርዳታ ፈንድ በተጠቀሰው ጊዜ ውስጥ ለታለመበት ዓላማ መዋሉን ማረጋገጥ እንዲሁም በተሰጠው ጊዜ ውስጥ ሪፖርት ማድረግ፣ ለጤናው ዘርፍ ስኬት አስተዋጽኦ የሚያደርጉ ዕቃዎችና አገልግሎቶችን አቅርቦትና አስተዳደርን ማመቻቸት የዳይሬክቶሬቱ ዓላማ ነው።
የንብረት አስተዳደር እና ጠቅላላ አገልግሎት ዳይሬክቶሬት የተለያዩ ድጋፎችንና አገልግሎቶችን መምራትና ማሰተባበር ላይ ይሰራል። እነዚህ አገልግሎቶች በጤና አገልግሎት ዕቅዱ አፈፃፀም ላይ ቁልፍ ሚና የሚጫወቱ ሲሆን በሚኒስቴር መሥሪያ ቤት የምርትና አገልግሎት የድጋፍ ሥርዓትን ለማዘመን ጥረት እየተደረገ ነው።
በዚህ ረገድ የተቋሙ ንብረት መቶ በመቶ በEFMIS ሥርዓት ውስጥ ሲሆን የትራንስፖርት ማከፋፈያ ስርዓቱ በፍሊት አስተዳደር ስርዓት መሠረት መመራቱንና ለደንበኞቹ ደህንነቱ የተጠበቀና ቀልጣፋ አገልግሎት መስጠቱን በማረጋገጥ የተገናኘ ስርዓት የመተግበር ሰራ እየተሰራ ነው።
ዘመናዊ የንብረት አስተዳደርን በመተግበር የተቋሙን የንብረት አስተዳደር ለማዘመን ምርትና አገልግሎቶችን ማከናወን።
በንብረት አስተዳደር ሚኒስቴር አመራር በኩል የደንበኞቻችን ታማኝ ባለሙያ መሆን