79ኛዉ የዓለም ጤና ጉባኤ በስዊዘርላንድ ጄኔቫ እየተካሄደ ይገኛል

WHA79


በጤና ሚኒስትር ዶ/ር መቅደስ ዳባ የተመራዉ የኢትዮጵያ ልዑካን ቡድን በጄኔቫ እየተካሄደ በለዉ 79ኛዉ የዓለም ጤና ጉባኤ ላይ እየተሳተፈ ይገኛል።


በጉባኤዉ ላይ ንግግር ያደረጉት የጤና ሚኒስትር ዶ/ር መቅደስ ዳባ በቅርቡ ይፋ የሆነዉ የህብረተሰብ ጤና ዳሰሳ ጥናት ግኝት መሰረት ኢትዮጵያ የእናቶችና ህጻናት ሞትን በመቀነስ ረገድ አመርቂ ዉጤት ማስመዝገቧን በመግለጽ በቀጣይም አለም አቀፍ የጤና ተደራሽነትን በማረጋገጥ ለመጀመሪያ ደረጃ ጤና ክብካቤ ከፍተኛ ትኩረት ተሰጥቶ ጠንካራ የጤና ስርዓት እንዲፈጠር በትጋት እንደሚሰራ አጽንኦት በመስጠት ተናግረዋል። 

ኢትዮጵያ እንደ ዓለም ጤና ጉባኤ ያሉ አለም አቀፍ መድረኮችን በመጠቀም የጤና ዲፕሎማሲን በማጠናከር ላይ ትገኛለች - የጤና ሚኒስትር ዶ/ር መቅደስ ዳባ 

WHA79

በጤና ሚኒስትር ዶ/ር መቅደስ ዳባ የተመራዉ የኢትዮጵያ ልዑክ ቡድን በ79 ነኛዉ የዓለም ጤና ጉባኤ ላይ ለመሳተፍ ስዊዘርላንድ ጄኔቫ ገብቷል።


ዶ/ር መቅደስ ለልዑካን ቡድኑ ኦሪየንቴሽን በሰጡት መድረክ እንደገለጹት ኢትዮጵያ በተለይም እንደ የዓለም ጤና ጉባኤ ያሉ አለም አቀፍ መድረኮችን በመጠቀም የጤና ዲፕሎማሲን በማጠናከር ላይ ትገኛለች ብለዋል። 


ኢትዮጵያ የዓለም ጤና ድርጅት አባል ሀገር እንደመሆኗ በጉባኤዉ በሚወሰኑ ዉሳኔዎችና ቀጣይ ስራዎች የራሷን ድርሻ እንደምትወጣ ዶ/ር መቅደስ ተናግረዋል።


ወቅታዊ የኢቦላና ሀንታ ቫይረስ ሁኔታን ጨምሮ ሌሎች የዓለማችን ስጋት የሆኑ ወርሽኞችን መከላከልና መቆጣጠር በዋናነት በጉባኤዉ ቀርበዉ ዉይይት እንደሚደረግበት ይጠበቃል።

የዲጂታል ጤና ዘርፍ መሪ (Champion) በመሆን የተሰጣቸዉን ኃላፊነት አስመልክቶ የአፍሪካ በሽታ መቆጣጠሪያ እና መከላከያ ማዕከል (Africa CDC) ዋና ዳይሬክተር ከሆኑት ከዶክተር ዣን ካሴያ ጋር ዉጤታማ  ውይይት አድርገዋል 

AI

በውይይታቸዉም በተለያዩ ቅድሚያ የሚሰጣቸው ጉዳዮች ላይ የመከሩ ሲሆን፤ በተለይም በአፍሪካ ሕብረት የሰው ሰራሽ አስተውሎት (AI) እና የዲጂታል ጤና ዘርፍ መሪ (Champion) በመሆን የተሰጣቸዉን አዲስ ኃላፊነት በሚመለከት በስፋት ተነጋግረዋል።


የፈጠራ ሥራዎች ለአፍሪካ ዕድገት ምንጊዜም ወሳኝ መሰረት ናቸዉ ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐብይ አህመድ በጤናው ዘርፍ የሚገጥመንን ተለዋዋጭ ተግዳሮቶች ለመወጣት የሰው ሰራሽ አስተውሎትንና የዲጂታል ቴክኖሎጂዎችን ዐቅም መጠቀም የጤና ሥርዓታችንን ለማጠናከር፣ ተደራሽነትን ለማስፋፋት እና ለሕዝባችን የተሻለ ውጤት ለማስመዝገብ ወሳኝ ነው ብለዋል። 

የአውሮፓ - የአፍሪካ ህብረት ለአፍሪካ ጤና አጋርነት ከ100 ሚሊዮን ዩሮ በላይ የድጋፍ ፓኬጆች ይፋ ሆኑ

EU-African Union

የአፍሪካን የጤና ደኅንነት፣ ጽናትና ሉዓላዊነት በማጠናከር ረገድ ትልቅ ምዕራፍ የሆነውን የአፍሪካ-አውሮፓ ህብረት የጤና አጋርነት የድጋፍ ፓኬጆች በሶስት አዳዲስ ኢኒሼቲቮች ላይ ትኩረት ያደረገ ነው ተብሏል።

ጠንካራ ስርዓት፣ ጠንካራ ተቋማት እና ለማህበረሰቡ የተሻሉ የጤና ውጤቶች እንዲመጡ ከአፍሪካ ሲዲሲ፣ ከአውሮፓ ህብረት እና ከሁሉም አጋሮች ጋር በቅርበት ለመስራት ኢትዮጵያ ሙሉ በሙሉ ቁርጠኛ ነች ብለዋል የጤና ሚኒስትር ዶ/ር መቅደስ ዳባ።

ሁለቱ አህጉራት የአፍሪካን የጤና ሉዓላዊነት እና ሰፊ የዘላቂ ልማት ግቦችን ለማሳካት ወቅታዊና የወደፊት የጤና ስጋቶችን ለመቅረፍ እየተደረገ ያለውን ጥረት በመቀጠል የአፍሪካ - የአውሮፓ ህብረት በአፍሪካ የበሽታ መቆጣጠሪያና መከላከያ ማእከል ሲዲሲ የረጅም ጊዜ እና አጠቃላይ የጤና አጋርነታቸውን አጠናክረው መቀጠላቸውን ጠቁመዋል።

በቅዱስ ጳውሎስ ሆስፒታል ሚሊኒየም ሜዲካል ኮሌጅ የአከርካሪ ቀዶ ህክምና ማዕከል /National spine center/ ስራ ጀመረ 

St. Paul

በቅዱስ ጳውሎስ ሆስፒታል ሚሊኒየም ሜዲካል ኮሌጅ ግቢ የተገነባዉ የአከርካሪ ቀዶ ህክምና ማዕከል /National spine center/ የጤና ሚኒስትር እና ሌሎች ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች ፣ በኢትዮጵያ የእስራኤል ም/አምባሳደር፣ የጄዲሲ መስራችና አንጋፋ የቀዶ ህክምና ባለሙያዎች የቅዱስ ጳውሎስ አመራሮች እንዲሁም በርካታ ባለድርሻ አካላት በተገኙበት ተመርቆ ስራ ጀምሯል።

የጤና ሚኒስቴር የህብረተስብ ጤና አደጋዎችና በሽታዎች አስቀድሞ መከላከልና መቆጣጠር ላይ ከአሜሪካ በሽታዎች መከላከልና መቆጣጠር (CDC) ጋር የትብብር ስራውን አጠናክሮ መቀጠል በሚቻልበት መንገድ ዙሪያ ዉይይት አድርገዋል

CDC

በውይይቱ ወቅት፣ የጤና ሚኒስትር ዶክተር መቅደስ ዳባ ከCDC ጋር ለረጅም ጊዜ የተገነባው ትብብር በጤና ስርአት ማጠናከር፣ በኤች አይ ቪ ኤድስና በወባ ፕሮግራሞች እንዲሁም በላብራቶሪ አቅም ግንባታ ዘርፍ ያስመዘገበውን ግልጽ ውጤት በማስታወስ ለተደረገው ድጋፍ አመስግነዋል።


በቀጣይም ይህ ትብብር በተለይ በድንገተኛ አደጋዎች ዝግጁነት እና ምላሽ አሰጣጥ ስርዓትን ማጠናከር እንዲሁም በክትባት አገልግሎት እና በመረጃ ስርዓት ማዘመን ዘርፎች ላይ በይበልጥ እንዲጠናከር ጠይቀዋል። 


የግሎባል ሄልዝ ሴንተር ሪጂናል ዳይሬክተር ማርታ አከርስ በበኩላቸው የአሜሪካ በሽታዎች መከላከልና መቆጣጠር (CDC) የኢትዮጵያ የጤና ስርአትን ለማጠናከር መስራቱን እንደሚቀጥል በመግለፅ፣ የጤና ሚኒስትር የትኩረት አቅጣጫዎች ላይ በተለይ በበለጠ ቅርበት አብረው እንደሚሰሩ አረጋግጠዋል።

የጤና ሚኒስትር ዶ/ር መቅደስ ዳባ ከካርተር ማዕከል ተወካዮች ጋር በኢትዮጵያ የጤና ዘርፍ የጋራ ጥረቶችን ለማጠናከር የሁለትዮሽ ውይይት አካሂደዋል

Minister

በስብሰባው ወቅት ሁለቱም ወገኖች በጤና ሚኒስቴር እና በድርጅቱ መካከል ያለውን የረጅም ጊዜ አጋርነት ገምግመዋል፡፡ በተለይም በበሽታ መከላከል፣ ክትትል እና ማጥፋት ፕሮግራም ዘርፎች፣ ትኩረት የሚሹ ሐሩራማ በሽታዎችን፣ የጊኒ ወርም በሽታን እና ሌሎች ቅድሚያ የሚሰጣቸውን የጤና ጉዳዮች ጨምሮ ለተገኘው እድገት ልዩ ትኩረት ተሰጥቷል።


ዶ/ር መቅደስ የካርተር ማዕከል እያደረገ ለሚገኘው ቀጣይነት ያለው ድጋፍ አድናቆታቸውን ገልጸው፤ ማእከሉ በመላ አገሪቱ የጤና ውጤቶችን ለማሻሻል ከፍተኛ አስተዋጽኦ እንዳደረገ መሆኑን ተናግረዋል። መንግስት ከልማት አጋሮች ጋር በቅርበት ለመስራት ያለውን ቁርጠኝነት ያስታወቁ ሲሆን፤ ጥራት ያላቸውን አገልግሎቶች ተደራሽነት ለማስፋት በትብብር መስራታቸውን እንደሚቀጥሉ ተናግረዋል።

ኢትዮጵያ የአደጋ ጊዜ የሕክምና ቡድን (EMT) አቅሟን በማጠናከር ዓለም አቀፍ የጤና አጋርነቷን እያሰፋች ነው

ACHIEVE Africa

የጤና ሚኒስቴር ከጀርመን ኤምባሲ፣ ከሮበርት ኮች ኢንስቲትዩት እና ከዓለም የጤና ድርጅት (WHO) ጋር የአደጋ ጊዜ የሕክምና ቡድኖች ተነሳሽነት እና አጋርነት በተመለከተ  የውይይት መድረክ ተካሂዷል።

በመድረኩ የጀርመን አምባሳደር ብርጊት ኦሪ ኢትዮጵያ የመጀመሪያውን ዓለም አቀፍ የአደጋ ጊዜ የሕክምና ቡድኖች  ዓለም አቀፍ ስብሰባ እንደምታስተናግድ አስታውቀዋል፣ ይህም አገሪቱ የተጠናከረ የአደጋ ጊዜ ምላሽ አቅም መገንባቷን እና የማርበርግ ቫይረስን ጨምሮ የቅርብ ጊዜ ወረርሽኞችን ውጤታማ በሆነ መንገድ መከላከል መቻሏን ማሳያ መሆኑን አስረድተዋል።

በ39ኛው የአፍሪካ ህብረት መደበኛ ጉባኤ የሚኒስትሮች የጎንዮሽ ስብሰባ በኢትዮጵያ በህጻናት ጤና እና በምግብ ዋስትና ረገድ የተመዘገቡ ስኬቶችን ማሳየት ችላለች

12

በአፍሪካ የህፃናት ጤና እና ስርዓተ-ምግብ ላይ ያተኮረው መድረክ የአፍሪካ ህብረት የስርዓተ-ምግብ ሻምፒዮን የሆኑት የሌሶቶ ግርማዊ ንጉሥ ሌቲ ሳልሳዊ፣ ከከፍተኛ የመንግስት ባለስልጣናትና ከዓለም አቀፍ ተቋማት ተወካዮች ተሳትፈዋል።

በዝግጅቱ ላይ ንግግር ያደረጉት በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ማዕረግ የዲሞክራሲ ግንባታ ማስተባበሪያ ማዕከል ኃላፊ አቶ አደም ፋራህ፣ ኢትዮጵያ የሌማት ቱሩፋት እና  የአረንጓዴ ሌጋሲ አስርት ዓመታት ተነሳሽነቶችን በተሳካ ሁኔታ በመተግበር ጉልህ ውጤቶችን ማስመዝገባን ተናግረዋል።

እንደ አቶ አደም ገለጻ፣ ፕሮግራሞቹ በመላ አገሪቱ የሚገኙ በሚሊዮን የሚቆጠሩ እናቶችንና ህጻናትን የተመጣጣኝ ምግብ አቅርቦትን በማሻሻልና የመቋቋም አቅምን በማጠናከር ተጠቃሚ አድረገዋል።

መንግስት የተመጣጠነ እና ደህንነቱ የተጠበቀ የምግብ አቅርቦትን ለማረጋገጥ ያለውን ቁርጠኝነት አረጋግጠው፣ ቀጣይነት ያለው ጥረት የወደፊት ትውልድ ደህንነትን ለመጠበቅ እንደሚያስችል አፅንዖት ሰጥተዋል።