Articles

የአፍሪካ የሕክምና ትምህርት (MedEDAfrica 2026) ኮንፈረንስ በስኬት ተጠናቀቀ!

MedEDAfrica 2026

በኢትዮጵያ አስተናጋጅነት በአዲስ አበባ ለሦስት ቀናት ሲካሄድ የቆየው የአፍሪካን የሕክምና ትምህርት ማዘመን ላይ ያተኮረው የ"MedEDAfrica 2026" ዓለም አቀፍ ኮንፈረንስ ዛሬ ተጠናቋል። 


በመዝጊያ ሥነ ሥርዓቱ የጤና ሚኒስትር ዴኤታ ወ/ሮ ሳህረላ አብዱላሂ የሕክምና ትምህርትን ማጠናከርና የጤና ባለሙያዎችን አቅም መገንባት የጤና አገልግሎት ጥራትና ደህንነትን ለማሻሻል ወሳኝ መሆኑን ገልጸው፣ ኢትዮጵያም የሥልጠና ጥራትንና የባለሙያዎችን ተደራሽነት ለማሳደግ በርካታ ተግባራትን እያከናወነች መሆኑን አስታውሰዋል።


ወ/ሮ ሳህረላ ኢትዮጵያ የጤና ባለሙያዎችን ቁጥር፣ ተደራሽነትና የሥልጠና ጥራት ለማሳደግ የተለያዩ ፕሮግራሞችን በመተግበር የጤና ሥርዓቱን እያጠናከረች መሆኑን ገልጸው፣ ከዚህ በተጨማሪም የጎረቤት ሀገራት የሕክምና ተማሪዎችን በሬዚደንሲ ፕሮግራም በማሰልጠን የክልሉን የጤና ሰው ኃይል ልማት እየደገፈች መሆኑን አስታውቀዋል።

"ጠንካራ የመጀመሪያ ደረጃ የጤና ክብካቤ ሥርዓቶችን ለመገንባት ዲጂታል ጤናን ጥቅም ላይ ማዋል" በሚል መሪ ሃሳብ ሶስተኛው የምስራቅ እና ደቡብ አፍሪካ ሃገራት የጤና መሪዎች የምክክር መድረክ በአዲስ አበባ መካሄድ ጀመረ 

Consultation Forum

ሦስተኛው ዓመታዊ አውደ ጥናት፤ በምሥራቅና ደቡብ አፍሪካ የሚገኙ ከፍተኛ የጤና፣ የገንዘብ እና  የኢንፎርሜሽንና የኮሙኒኬሽን ቴክኖሎጂ (ICT) ባለሥልጣናትን በመሰብሰብ አገራዊ ትብብርን ለማጠናከርና የጋራ የመማማሪያ መረብ ለመፍጠር ያለመ ነው። 


የአውደ ጥናቱ ዋና ዓላማ ይበልጥ ፍትሃዊ፣ ጠንካራ እና በበጀት ረገድ ዘላቂነት ያለው የመጀመሪያ ደረጃ የጤና ሥርዓት ለመገንባት የሚያስችል የጋራ ቀጠናዊ የዲጂታል ጤና ራዕይን ማምጣት መሆኑን ያስረዱት የጤና ሚኒስትር ዶ/ር መቅደስ ዳባ ናቸው።


 ተሳታፊዎቹ በየአገራቱ ያለውን ተሞክሮ፣ የአፈጻጸም ማነቆዎችን እና የዲጂታል ጤና መፍትሔዎችን በሰፊው ተግባራዊ ለማድረግ የተገኙ ትምህርቶችን ይለዋወጣሉ፤ እንዲሁም ቴክኖሎጂ የጤና የሰው ኃይል አስተዳደርን እና የመረጃ ውህደትን እንዴት እንደሚያሳድግ ያላቸውን ቴክኒካዊ ግንዛቤ ያሳድጋሉ ሲሉ ሚኒስትሯ ተናግረዋል። 

የአፍሪካ የሕክምና ትምህርት «MedEDAfrica 2026» አህጉራዊ ጉባኤ በአዲስ አበባ መካሄድ ጀመረ

MedEDAfrica 2026

ኢትዮጵያ በሕክምና ትምህርትና በዲጂታል ፈጠራ የአህጉራችንን የነገ ተስፋ ለመቅረጽ በቁርጠኝነት እየሠራች እንደምትገኝ የገለፁት ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ክቡር አቶ ተመስገን ጥሩነህ ናቸው።

ሀገራችን ከራሷ አልፋ ከአፍሪካ ሀገራት የመጡ የጤና ባለሞያዎችን በከፍተኛ የሕክምና ትምህርት ተቋሞቿ በማስተማር እንደ ቀጣናዊ የልቀት ማዕከል እያገለገለች ትገኛለች ያሉት ክቡር አቶ ተመስገን፣ በክቡር ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አሕመድ መሪነት ሀገራችን በሰው ሠራሽ አስተውሎት እና በዲጂታል ፈጠራ የአህጉሪቱ ተምሳሌት ለመሆን ራሷን እያዘጋጀችም ነው ብለዋል። 

በአፍሪካ አህጉራችን ውስጥ የሚገኙ ዩኒቨርሲቲዎቻችን፣ ሆስፒታሎቻችን እና የኢንዱስትሪው ዘርፍ በጋራ ሊሠሩ፣ የምርምር ውጤቶችም የፖሊሲ መመሪያ ሊሆኑና የሕዝቡን ሕይወት በተግባር ሊለውጡ ይገባል ብለዋል ክቡር አቶ ተመስገን።