Articles

የመንገድ ደህንነትና መድን ፈንድ አገልግሎት የተሽከርካሪ አደጋ ተጎጂዎች የአስቸኳይ ህክምና አገልግሎት አፈፃፀም እረቂቅ መመሪያ ላይ የሕዝብ አስተያየት ለመሰብሰብ የወጣ ማስታወቂያ

የትራንስፖርት እና ሎጂስቲክስ ሚኒስቴር የተሽከርካሪ አደጋ የሶስተኛ ወገን መድን አዋጅ ቁጥር 799/2005 አንቀጽ 22 ንዑስ አንቀጽ 1 በተሰጠው ስልጣን እና በአንቀጽ 27 ንዑስ አንቀጽ 3 በተደነገገው መሠረት በተሽከርካሪ አደጋ ጉዳት የደረሰበት ማንኛውም ሰው አስቸኳይ የህክምና እገልግሎት እንዲያገኝ የመንገድ ደህንነትና መድን ፈንድ አገልግሎት  የተሽከርካሪ አደጋ ተጎጂዎች የአስቸኳይ ህክምና አገልግሎት አፈፃፀም እረቂቅ መመሪያ ተዘጋጅቷል፡፡

ረቂቅ መመሪያው ላይ አስተያየት መስጠት የሚፈልግ ማንኛውም ሰው እስከ ጥር 05/2017 ዓ.ም ድረስ አስተያየቱን ታች ባለው ቅፅ በመሙላት ወይንም በሚኒስቴሩ መስሪያ ቤት ሜዲካል አገልግሎት መሪ ሥራ አስፈፃሚ በአካል በመገኘት ማስገባት ይችላል፡፡

የተሽከርካሪ አደጋ ተጎጂዎች አስቸኳይ ህክምና እና የካሳ አፈፃፀም መመሪያ ላይ የሕዝብ አስተያየት ለመሰብሰብ

የተሸከርካሪ አደጋ ተጎጅዎች የሶስተኛ ወገን መድን አዋጅ 799/2005 ዓ.ም በጸደቀው መሰረት በሁሉም ጤና ተቋማት እስከ ሁለት ሺህ ብር አገልግሎት በነፃ እንዲያገኙ ተደንግጓል፡፡ ይህንም አዋጅ መሰረት በማድረግ በተሻሻለው በደንብ ቁጥር 554/2016 የድንገተኛ ህክምና ወጪ እስከ አስራ አምስት ሺህ ብር እንዲሻሻል የተደረገ ሲሆን ለዚህም እረቂቅ መመሪያ በመንገድ ደህንነትና መድን ፈንድ አገልግሎት ተዘጋጅቷል፡፡

በእረቂቅ መመሪያው ላይ አስተያየት መስጠት የሚፈልግ ማንኛውም ሰው እስከ ጥር 05/2017 ዓ.ም ድረስ አስተያየቱን ታች ባለው ቅፅ በመሙላት ወይንም በሚኒስቴሩ መስሪያ ቤት ሜዲካል አገልግሎት መሪ ሥራ አስፈፃሚ በአካል በመገኘት ማስገባት ይችላል፡፡

መድሃኒት የተላመዱ ተህዋስያን የሚያስከትሉትን ጉዳት ለመቀነስ  ኢትዮጵያ ትኩረት ሰጥታ ትሰራለች፣ የጤና ሚኒስትር ዶ/ር መቅደስ ዳባ 

Dr. Mekdes Daba

በተባበሩት መንግስታት ዋና መስሪያ ቤት እየተካሄደ በሚገኘው የተባበሩት መንግስታት ድርጅት 79ኛው ጠቅላላ ጉባኤ ላይ የጤና ሚኒስትር ዶ/ር መቅደስ ዳባ ኢትዮጵያ መድሃኒት የተላመዱ ተህዋስያን የሚያስከትሉትን ጉዳት ለመቀነስ ትኩረት ሰጥታ እንደምትሰራ ገለጸዋል።


በመድሃኒት የተላመዱ ተህዋስያን ዙሪያ ለመምከር በተዘጋጀው የከፍተኛ ሃላፊዎች መድረክ ላይ ንግግር ያደረጉት ዶ/ር መቅደስ ኢትዮጵያ መድሃኒት የተላመዱ ተህዋስያን የሚያስከትሉትን ተጽእኖ ለመቀነስ በቁርጠኝነት እንደምትሰራና ለዚህም የግንዛቤ ማስጨበጫ ስራዎች፣ አስፋላጊውን ክትትል ማድረግና የምርምር ስራዎችን እንደምታጠናክር ገልጸዋል።  ይህ ዓለም አቀፋዊ ስጋት ዓለም አቀፍ ትብብርን የሚጠይቅ መሆኑን ሚኒስተሯ አስምረውበታል።