Articles

የጤና ሚኒስትር ዶ/ር መቅደስ ዳባ ከአሜሪካ ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ምክትል ረዳት ጸሐፊ ዶ/ር ማማዲ ይላ ጋር በመንግስት ለመንግስት  የሚሰሩ የጤና ጉዳዮች ዙሪያ ተወያዩ

Dr Mekdes Daba

የጤና ሚኒስትር ዶ/ር መቅደስ ዳባ፣ የኢትዮጵያ እና የአሜሪካ መንግስታት በጤናዉ ዘርፍ ዘርፈብዙ የትብብር ስራዎችን ለረጅም ግዜ በጋራ እያከናወኑ መሆኑን ገልጸዉ በተለይም  የዲጂታል ጤና አገልግሎትን በማስፋፋት፣ የወባ ወረርሽኝን በመከላከል፣ የእናቶችና ህጻናትን ጤና በመጠበቅ እንዲሁም የቲቢ እና የኤች.አይ.ቪ/ኤድስ ስርጭትን በመግታት ረገድ ዉጤቶች መገኘቱን ተናግረዋል።


​በቀጣይም የመጀመሪያ ደረጃ የጤና ክብካቤ አገልግሎትን  በማጎልበት ጠንካራ የጤና ስርዓትን ለመፍጠር  ዘላቂ የጤና ልማት ግቦችን ሙሉ በሙሉ ለማሳካት ኢትዮጵያ እያደረገች ያለዉን ጥረት አሜሪካ እያደረገች ያለዉን ድጋፍ  አጠናክራ እንድትቀጥል ጠይቀዋል። 

በስዊዘርላንድ ጄኔቫ እየተካሄደ ባለዉ የዓለም ጤና ጉባኤ የጎንዮሽ መድረኮች በተለያዩ የጤና ርዕሰ ጉዳዮች ላይ ዉይይት ተካሂዷል

#WHA79

በስዊዘርላንድ ጄኔቫ እየተካሄደ ባለዉ የዓለም ጤና ጉባኤ የጎንዮሽ መድረኮች የኢትዮጵያ ልዑካን ቡድን በተገኙበት በተለያዩ ጤና ርዕሰ ጉዳዮች ላይ ዉይይት ተካሂዷል።

ኢትዮጵያ ከሩዋንዳ፣ ጊኒ፣ ኔፓል፣ እና አጋር አካላት ጋር በትብብር ባዘጋጀችዉ የጎንዮሽ መድረክ የድንገተኛ፣ ቀዶጥገና ህክምና አገልግሎትን በተመለከተ የጤና ሚኒስትር ዶ/ር መቅደስ ዳባ የኢትዮጵያን ተሞክሮ ባጋሩት ገለጻ ታካሚን ማእክል ያደረገ የድንገተኛ ቀዶጥገና ህክምና አገልግሎት ማጠናከርና ተደራሽ ማድረግ ሁለንተናዊ የጤና ሽፋንና የጤና ዋስትናን ለማረጋገጥ በጣም አስፈላጊ መሆኑን ተናግረዋል።

ኢትዮጵያና ባርቤዶስ በጤናው ዘርፍ በጋራ ለመስራት የሚያስችላቸውን ስምምነት ተፈራረሙ

#WHA79

ኢትዮጵያና ባርቤዶስ በካሪኮም የትብብር ማእቀፍ በቀጠናው ባሉ ሀገራት መካከል በትብብር ለመስራት በሁለቱ ሀገራት መሪዎች በተደረሰዉ ስምምነት መሰረት እና ማእቀፍ መነሻ በማድረግ የተለያዩ ስራዎች እየተሰሩ ይገኛል።


የዚሁ ትብብር መስክ አካል የሆነ በጄኒቫ እየተካሄደ ከሚገኘው የዓለም የጤና ጉባኤ #WHA79 ጎን ለጎን በጤናው ዘርፍ በጋራ ለመስራት የሚያስችል ስምምነት በሁለቱ ሀገራት የጤና ሚኒስትሮች የተፈረመ ሲሆን ስምምነቱ በዋናነት በሀገራቱ መካከል የአቅም ግንባታ እና ክህሎት ሽግግር፤ የባለሙያዎች ትብብርና በተለያዩ የጤና ጉዳዮች ላይ በትብብር ለመስራት ታሳቢ ያደረገ ሲሆን በተጨማሪም በሁለቱ ሀገራት መካከል ያለውን የህዝብ ለህዝብ ግንኙነት ለማጠናከር እንደሚረዳም ይታመናል።