የጤና ሚኒስትር ዶ/ር መቅደስ ዳባ ከአሜሪካ ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ምክትል ረዳት ጸሐፊ ዶ/ር ማማዲ ይላ ጋር በመንግስት ለመንግስት የሚሰሩ የጤና ጉዳዮች ዙሪያ ተወያዩ
የጤና ሚኒስትር ዶ/ር መቅደስ ዳባ፣ የኢትዮጵያ እና የአሜሪካ መንግስታት በጤናዉ ዘርፍ ዘርፈብዙ የትብብር ስራዎችን ለረጅም ግዜ በጋራ እያከናወኑ መሆኑን ገልጸዉ በተለይም የዲጂታል ጤና አገልግሎትን በማስፋፋት፣ የወባ ወረርሽኝን በመከላከል፣ የእናቶችና ህጻናትን ጤና በመጠበቅ እንዲሁም የቲቢ እና የኤች.አይ.ቪ/ኤድስ ስርጭትን በመግታት ረገድ ዉጤቶች መገኘቱን ተናግረዋል።
በቀጣይም የመጀመሪያ ደረጃ የጤና ክብካቤ አገልግሎትን በማጎልበት ጠንካራ የጤና ስርዓትን ለመፍጠር ዘላቂ የጤና ልማት ግቦችን ሙሉ በሙሉ ለማሳካት ኢትዮጵያ እያደረገች ያለዉን ጥረት አሜሪካ እያደረገች ያለዉን ድጋፍ አጠናክራ እንድትቀጥል ጠይቀዋል።