Articles

በ39ኛው የአፍሪካ ህብረት መደበኛ ጉባኤ የሚኒስትሮች የጎንዮሽ ስብሰባ በኢትዮጵያ በህጻናት ጤና እና በምግብ ዋስትና ረገድ የተመዘገቡ ስኬቶችን ማሳየት ችላለች

12

በአፍሪካ የህፃናት ጤና እና ስርዓተ-ምግብ ላይ ያተኮረው መድረክ የአፍሪካ ህብረት የስርዓተ-ምግብ ሻምፒዮን የሆኑት የሌሶቶ ግርማዊ ንጉሥ ሌቲ ሳልሳዊ፣ ከከፍተኛ የመንግስት ባለስልጣናትና ከዓለም አቀፍ ተቋማት ተወካዮች ተሳትፈዋል።

በዝግጅቱ ላይ ንግግር ያደረጉት በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ማዕረግ የዲሞክራሲ ግንባታ ማስተባበሪያ ማዕከል ኃላፊ አቶ አደም ፋራህ፣ ኢትዮጵያ የሌማት ቱሩፋት እና  የአረንጓዴ ሌጋሲ አስርት ዓመታት ተነሳሽነቶችን በተሳካ ሁኔታ በመተግበር ጉልህ ውጤቶችን ማስመዝገባን ተናግረዋል።

እንደ አቶ አደም ገለጻ፣ ፕሮግራሞቹ በመላ አገሪቱ የሚገኙ በሚሊዮን የሚቆጠሩ እናቶችንና ህጻናትን የተመጣጣኝ ምግብ አቅርቦትን በማሻሻልና የመቋቋም አቅምን በማጠናከር ተጠቃሚ አድረገዋል።

መንግስት የተመጣጠነ እና ደህንነቱ የተጠበቀ የምግብ አቅርቦትን ለማረጋገጥ ያለውን ቁርጠኝነት አረጋግጠው፣ ቀጣይነት ያለው ጥረት የወደፊት ትውልድ ደህንነትን ለመጠበቅ እንደሚያስችል አፅንዖት ሰጥተዋል።

የአፍሪካን የክትባት እና የሕክምና ሉዓላዊነትን ለማረጋገጥ ያለመው ግዙፉ "ACHIEVE Africa" የተሰኘ ኢኒሼቲቭ ከ39ኛው የአፍሪካ ህብረት የመሪዎች ጉባኤ ጎን ለጎን በይፋ ተመሠርቷል 

Dr Mekdes Daba

​በኢኒሼቲቩ ማስጀመሪያ መርሃ-ግብር ላይ የተገኙት የጤና ሚኒስትር ዶ/ር መቅደስ ዳባ፤ ኢትዮጵያ የአፍሪካ ህብረት እ.ኤ.አ በ2040 የክትባት ፍላጎትን 60 በመቶ በአህጉር ውስጥ ለማሟላት ያስቀመጠውን ግብ ለማሳካት ግንባር ቀደም ሚና እየተጫወተች መሆኑን የገለጹ ሲሆን መንግስት የመድኃኒት ግዥ ስርዓቱን በአገር ውስጥ ለሚመረቱ ምርቶች ቅድሚያ እንዲሰጥ በማሻሻሉ፣ በዘርፉ የአገር ውስጥ ፍላጎትን ሽፋን ከ8 በመቶ ወደ 42 በመቶ ማደጉን ጠቁመው በቀጣይ አምስት ዓመታት ወደ 60 በመቶ ለማሳደግ ታቅዶ በትኩረት እየተሰራ መሆኑንም አረጋግጠዋል።
\
​ኢትዮጵያን የፈጠራ ማዕከል (Innovation Hub) ለማድረግ ሰፊ ስራዎች እየተሰሩ መሆኑን የገለጹት ዶ/ር መቅደስ የሀገሪቱ የክትባት የማምረት ጉዞ አሁን ላይ "ይሳካል ወይ?" የሚለው ጥያቄ ቀርቶ "እንዴት እና በምን ፍጥነት?" ወደሚለው ወሳኝ ምዕራፍ መሸጋገሩን አስታውሰዋል። 

ከመላው አፍሪካ የተውጣጡ የጤና ሚኒስትሮች እና ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች የአፍሪካ ህብረት የመሪዎች ጉባኤ የጎንዮሸ ስብሰባ መካሄድ ጀምሯል

Dr Mekdes Daba

"የአፍሪካን የጤና ደህንነት እና የሉዓላዊነት አጀንዳ ማራመድ፡ ቁርጠኛ ፋይናንስ እና አመራርን በመጠቀም ዘላቂነትን ማረጋገጥ" በሚል መሪ ቃል የአፍሪካን የጤና ስርዓቶች በዘላቂ ፋይናንስ፣ ጠንካራ አመራር እና በራስ መተማመንን ለማረጋገጥ በተሻለ አህጉራዊ ትብብርን ማጠናከር ላይ ያተኮረ የጎንዪሽ  ስብሰባ በአፍሪካ የበሽታ መቆጣጠሪያ እና መከላከያ ማዕከል( Africa CDC) እየተካሄደ ይገኛል። 

በስብሰባው ላይ የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የኢፌድሪ የጤና ሚኒስትር እና በአፍሪካ የበሽታ መቆጣጠሪያ እና መከላከያ ማዕከል( Africa CDC) የቦርድ ም/ሰብሳቢ ዶ/ር መቅደስ ዳባ ዝግጅቱን “የአመራር ቁርጠኝነት ማሳያ” ሲሉ ገልጸውታል። ስብሰባው በአፍሪካ አገሮች መካከል ያለውን የጤና ደህንነት እና ሉዓላዊነት ለማሳደግ ያለንን የጋራ ቁርጠኝነት የሚያንፀባርቅ መሆኑን ተናግረዋል።