Articles

ከመላው አፍሪካ የተውጣጡ የጤና ሚኒስትሮች እና ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች የአፍሪካ ህብረት የመሪዎች ጉባኤ የጎንዮሸ ስብሰባ መካሄድ ጀምሯል

Dr Mekdes Daba

"የአፍሪካን የጤና ደህንነት እና የሉዓላዊነት አጀንዳ ማራመድ፡ ቁርጠኛ ፋይናንስ እና አመራርን በመጠቀም ዘላቂነትን ማረጋገጥ" በሚል መሪ ቃል የአፍሪካን የጤና ስርዓቶች በዘላቂ ፋይናንስ፣ ጠንካራ አመራር እና በራስ መተማመንን ለማረጋገጥ በተሻለ አህጉራዊ ትብብርን ማጠናከር ላይ ያተኮረ የጎንዪሽ  ስብሰባ በአፍሪካ የበሽታ መቆጣጠሪያ እና መከላከያ ማዕከል( Africa CDC) እየተካሄደ ይገኛል። 

በስብሰባው ላይ የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የኢፌድሪ የጤና ሚኒስትር እና በአፍሪካ የበሽታ መቆጣጠሪያ እና መከላከያ ማዕከል( Africa CDC) የቦርድ ም/ሰብሳቢ ዶ/ር መቅደስ ዳባ ዝግጅቱን “የአመራር ቁርጠኝነት ማሳያ” ሲሉ ገልጸውታል። ስብሰባው በአፍሪካ አገሮች መካከል ያለውን የጤና ደህንነት እና ሉዓላዊነት ለማሳደግ ያለንን የጋራ ቁርጠኝነት የሚያንፀባርቅ መሆኑን ተናግረዋል። 

በኢትዮጵያ በስርዓተ-ምግብ ማሻሻያ እርምጃዎች በተሰራዉ ስራ ተምሳሌት የሚሆን ዉጤት ተገኝቷል - የሌሴቶ ንጉስ ግርማዊ ሌቲ ሳልሳዊ

nutrition

የሌሴቶ ንጉስ ግርማዊ ሌቲ ሳልሳዊ ከጤና ሚኒስትር ዶ/ር መቅደስ ዳባ ጋር በአዲስ አበባ በሚገኘው ዘውዲቱ መታሰቢያ ሆስፒታል የህፃናት እንክብካቤ እና የስርዓተ-ምግብ ክፍልን ጎብኝተዋል፣ በጉብኝታቸው ኢትዮጵያ የእናቶችን እና የህፃናትን ጤና ለማሻሻል ያላትን ቁርጠኝነት አድንቀዋል።

በጉብኝቱ ወቅት ንግግር ያደረጉት ግርማዊ ንጉስ ሌቲ “ውጤታማ የስርዓተ-ምግብ እርምጃ ህይወትን ያድናሉ” በማለት አፅንኦት ሰጥተው፤ በኢትዮጵያ  በስርዓተ-ምግብ ማሻሻያ እርምጃዎች በተሰራዉ ስራ ተምሳሌት የሚሆን ዉጤት ተገኝቷል ብለዋል። ስርዓተ-ምግብ በሽታን በመከላከል እና የህፃናትን ሞት በመቀነስ ረገድ ያለውን ወሳኝ ሚናም ገልጸዋል። 

ንጉሱ እንዳሉት ኢትዮጵያ እናቶችን እና ህፃናትን ለመጠበቅ የምታደርገውን ጠንካራ ጥረት በገዛ ዓይናቸው ለማየት መቻላቸውን ተናግረው፤ አገሪቱ ስርዓተ-ምግብን ከጤና አጠባበቅ አደረጃጀቷ ጋር በማዋሃድ ዘላቂ የጤና ውጤቶችን ለማሳካት የሚያስመሰግን እና ስትራቴጂካዊ አቀራረብ መከተሏን ገልጸዋል።

ኢትዮጵያ የማርበርግ ቫይረስ በሽታን በመቆጣጠር ረገድ ስኬታማ ሆናለች 

Dr Mekdes Daba

ኢትዮጵያ የማርበርግ ቫይረስን በመቆጣጠር ያደረገችው ስኬታማ ጥረት በጠንካራ አመራር፣ ፈጣን ምላሽ እና በተቀናጀ እርምጃ ትልቅ የህብረተሰብ ጤና ስኬትን ማስመዝገቧን የኤፌዴሪ የተወካዮች ምክር ቤት አፈጉባኤ የተከበሩ ታገሰ ጫፎ ገልፀው፤ ስኬቱ የጤና ፖሊሲ፣ የጤና ባለሙያዎች፣ እና ባለድርሻ አካላት የጋራ የመተባበር እና የመደመር ውጤት ነው ብለዋል።
 
የጤና ሚኒስትር ዶ/ር መቅደስ ዳባ  በሃገራችን የጤና ታሪክ ትልቅ የስኬት አሻራ የጣለ ተሞክሮ መሆኑን ገልፀው፤ ማህበረሰቡን በማስተባበር ፈጣን ምላሽ በመስጠት ቫይረሱ ሊያደርስ የሚችለውን ጉዳት መቀነስ መቻሉን ተናግረዋል።