Articles

የጤና ሚኒስቴር የህብረተስብ ጤና አደጋዎችና በሽታዎች አስቀድሞ መከላከልና መቆጣጠር ላይ ከአሜሪካ በሽታዎች መከላከልና መቆጣጠር (CDC) ጋር የትብብር ስራውን አጠናክሮ መቀጠል በሚቻልበት መንገድ ዙሪያ ዉይይት አድርገዋል

CDC

በውይይቱ ወቅት፣ የጤና ሚኒስትር ዶክተር መቅደስ ዳባ ከCDC ጋር ለረጅም ጊዜ የተገነባው ትብብር በጤና ስርአት ማጠናከር፣ በኤች አይ ቪ ኤድስና በወባ ፕሮግራሞች እንዲሁም በላብራቶሪ አቅም ግንባታ ዘርፍ ያስመዘገበውን ግልጽ ውጤት በማስታወስ ለተደረገው ድጋፍ አመስግነዋል።


በቀጣይም ይህ ትብብር በተለይ በድንገተኛ አደጋዎች ዝግጁነት እና ምላሽ አሰጣጥ ስርዓትን ማጠናከር እንዲሁም በክትባት አገልግሎት እና በመረጃ ስርዓት ማዘመን ዘርፎች ላይ በይበልጥ እንዲጠናከር ጠይቀዋል። 


የግሎባል ሄልዝ ሴንተር ሪጂናል ዳይሬክተር ማርታ አከርስ በበኩላቸው የአሜሪካ በሽታዎች መከላከልና መቆጣጠር (CDC) የኢትዮጵያ የጤና ስርአትን ለማጠናከር መስራቱን እንደሚቀጥል በመግለፅ፣ የጤና ሚኒስትር የትኩረት አቅጣጫዎች ላይ በተለይ በበለጠ ቅርበት አብረው እንደሚሰሩ አረጋግጠዋል።

የጤና ሚኒስትር ዶ/ር መቅደስ ዳባ ከካርተር ማዕከል ተወካዮች ጋር በኢትዮጵያ የጤና ዘርፍ የጋራ ጥረቶችን ለማጠናከር የሁለትዮሽ ውይይት አካሂደዋል

Minister

በስብሰባው ወቅት ሁለቱም ወገኖች በጤና ሚኒስቴር እና በድርጅቱ መካከል ያለውን የረጅም ጊዜ አጋርነት ገምግመዋል፡፡ በተለይም በበሽታ መከላከል፣ ክትትል እና ማጥፋት ፕሮግራም ዘርፎች፣ ትኩረት የሚሹ ሐሩራማ በሽታዎችን፣ የጊኒ ወርም በሽታን እና ሌሎች ቅድሚያ የሚሰጣቸውን የጤና ጉዳዮች ጨምሮ ለተገኘው እድገት ልዩ ትኩረት ተሰጥቷል።


ዶ/ር መቅደስ የካርተር ማዕከል እያደረገ ለሚገኘው ቀጣይነት ያለው ድጋፍ አድናቆታቸውን ገልጸው፤ ማእከሉ በመላ አገሪቱ የጤና ውጤቶችን ለማሻሻል ከፍተኛ አስተዋጽኦ እንዳደረገ መሆኑን ተናግረዋል። መንግስት ከልማት አጋሮች ጋር በቅርበት ለመስራት ያለውን ቁርጠኝነት ያስታወቁ ሲሆን፤ ጥራት ያላቸውን አገልግሎቶች ተደራሽነት ለማስፋት በትብብር መስራታቸውን እንደሚቀጥሉ ተናግረዋል።

ኢትዮጵያ የአደጋ ጊዜ የሕክምና ቡድን (EMT) አቅሟን በማጠናከር ዓለም አቀፍ የጤና አጋርነቷን እያሰፋች ነው

ACHIEVE Africa

የጤና ሚኒስቴር ከጀርመን ኤምባሲ፣ ከሮበርት ኮች ኢንስቲትዩት እና ከዓለም የጤና ድርጅት (WHO) ጋር የአደጋ ጊዜ የሕክምና ቡድኖች ተነሳሽነት እና አጋርነት በተመለከተ  የውይይት መድረክ ተካሂዷል።

በመድረኩ የጀርመን አምባሳደር ብርጊት ኦሪ ኢትዮጵያ የመጀመሪያውን ዓለም አቀፍ የአደጋ ጊዜ የሕክምና ቡድኖች  ዓለም አቀፍ ስብሰባ እንደምታስተናግድ አስታውቀዋል፣ ይህም አገሪቱ የተጠናከረ የአደጋ ጊዜ ምላሽ አቅም መገንባቷን እና የማርበርግ ቫይረስን ጨምሮ የቅርብ ጊዜ ወረርሽኞችን ውጤታማ በሆነ መንገድ መከላከል መቻሏን ማሳያ መሆኑን አስረድተዋል።