ኢትዮጵያና ባርቤዶስ በጤናው ዘርፍ በጋራ ለመስራት የሚያስችላቸውን ስምምነት ተፈራረሙ

  • Time to read less than 1 minute
#WHA79

ኢትዮጵያና ባርቤዶስ በካሪኮም የትብብር ማእቀፍ በቀጠናው ባሉ ሀገራት መካከል በትብብር ለመስራት በሁለቱ ሀገራት መሪዎች በተደረሰዉ ስምምነት መሰረት እና ማእቀፍ መነሻ በማድረግ የተለያዩ ስራዎች እየተሰሩ ይገኛል።


የዚሁ ትብብር መስክ አካል የሆነ በጄኒቫ እየተካሄደ ከሚገኘው የዓለም የጤና ጉባኤ #WHA79 ጎን ለጎን በጤናው ዘርፍ በጋራ ለመስራት የሚያስችል ስምምነት በሁለቱ ሀገራት የጤና ሚኒስትሮች የተፈረመ ሲሆን ስምምነቱ በዋናነት በሀገራቱ መካከል የአቅም ግንባታ እና ክህሎት ሽግግር፤ የባለሙያዎች ትብብርና በተለያዩ የጤና ጉዳዮች ላይ በትብብር ለመስራት ታሳቢ ያደረገ ሲሆን በተጨማሪም በሁለቱ ሀገራት መካከል ያለውን የህዝብ ለህዝብ ግንኙነት ለማጠናከር እንደሚረዳም ይታመናል።