ኢትዮጵያና ባርቤዶስ በካሪኮም የትብብር ማእቀፍ በቀጠናው ባሉ ሀገራት መካከል በትብብር ለመስራት በሁለቱ ሀገራት መሪዎች በተደረሰዉ ስምምነት መሰረት እና ማእቀፍ መነሻ በማድረግ የተለያዩ ስራዎች እየተሰሩ ይገኛል።
የዚሁ ትብብር መስክ አካል የሆነ በጄኒቫ እየተካሄደ ከሚገኘው የዓለም የጤና ጉባኤ #WHA79 ጎን ለጎን በጤናው ዘርፍ በጋራ ለመስራት የሚያስችል ስምምነት በሁለቱ ሀገራት የጤና ሚኒስትሮች የተፈረመ ሲሆን ስምምነቱ በዋናነት በሀገራቱ መካከል የአቅም ግንባታ እና ክህሎት ሽግግር፤ የባለሙያዎች ትብብርና በተለያዩ የጤና ጉዳዮች ላይ በትብብር ለመስራት ታሳቢ ያደረገ ሲሆን በተጨማሪም በሁለቱ ሀገራት መካከል ያለውን የህዝብ ለህዝብ ግንኙነት ለማጠናከር እንደሚረዳም ይታመናል።