የምስራቅ አፍሪካ ሀገራት የቲቢ በሽታን ለመከላከልና ለመቆጣጠር በጋራ ሊሰሩ ይገባል

EGAD

16ኛው አመታዊ የቲቢ ምርምር ጉባኤ ላይ ከተገኙ የአጎራባች ሃገራት ተወካዮችጋር የቲቢ በሽታን መከላከልና መቆጣጠር በተመለከተ የጎንዮሽ ውይይት ተካሂዷል።

አጎራባች ሀገራት በሚዋሰኑባቸው አከባቢዎች ተመሳሳይ ማህበረሰብ የሚገኝባቸው በመሆናቸው እና በተለይም አርብቶ አደር በሚበዛባቸው የምስራቅ አፍሪካ አጎራባች አከባቢዎች የቲቢ በሽታ ህክምናን ለመስጠትም ሆነ ክትትል ለማድረግ አዳጋች በመሆኑ ሃገራቱ በጋራ መስራታቸው ጠቀሜታው የጎላ ይሆናል።

በአጎራባች አከባቢዎች ያለው ነባራዊ ሁኔታን የሚያመለክት በቂ መረጃ አለመኖር እና የግብአት ውስንነት ማነቆ መሆኑን ተወካዮች አውስተው የምርምር ተግባራትን በስፋት መስራት፣ ትብብርን ማጠናከርና ለጉዳዩ ትኩረት እንዲሰጥ ከፍተኛ ሃላፊዎችን ማስገንዘብና የሚድያና ተግባቦት ፕላትፎርም ተፈጥሮ በትኩረት በጋራ መስራት አስፈላጊ እንደሆነ ጠቁመዋል።

አስራ ስድስተኛው የቲቢ ምርምር ጉባኤ በሀዋሳ ከተማ ተጀምሯል

TB research

አመታዊ ብሔራዊ የቲቢ ምርምር ጉባኤ በዚህ አስቸጋሪ ወቅት መደረጉ ጠቀሜታው የጎላ ነው ያሉት የጤና ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴኤታ ዶ/ር አየለ ተሾመ አገራች ኢትዮጵያ በተከሰተው ጦርነት እና የተለያዩ ግጭቶች ምክንያት በጤና ተቋማት ላይ የደረሰው ውድመቶች እና የጤና ተቋማት መስተጓጎል፤ የህዝብ መፈናቀል፤ የድርቅ መስፋፋት እና በኮቪድ 19 ወረርሽኝ ምክንያቶች በቲቢ በሽታ መከላከል እና ቁጥጥር ላይ የተመዘገቡ ስኬቶች እንዳይቀለበሱ በቁርጠኝነት ልንሰራ ይገባል ብለዋል፡፡ 


በየአመቱ በሚካሄደው የቲቢ ምርምር ጉባኤ ላይ የሚቀርቡ የምርምር ሥራዎች የቲቢ በሽታን በመከላከልና በመቆጣጠር ረገድ ከፍተኛ አስተዋፅኦ እያደረገ እንደሆነ ተናግረዋል፡፡ 
አገራች ኢትዮጵያ የቲቢ በሽታ ስርጭት ለመግታትና ቲቢ ለማጥፋት ዘመናዊ የምርመራ መሳሪያዎችን በጤና ተቋማት በማስገባት አገልግሎቱ ተደራሽ በማድረግና በየአምስት አመቱ የሚተገበር እቅድ በማዘጋጀት እየተሰራ ነው ተብሏል፡፡ 

በህግ ማስከበር እና በህልውና ዘመቻው አስተዋጽኦ ላበረከቱ የጤናው ዘርፍ አካላት ምስጋናና እውቅና ተሰጣቸው

Gratitude and recognition program

በሃገራችን በተካሄደው በህግ ማስከበር እና በህልውና ዘመቻው ላይ አስተዋጽኦ ላበረከቱ ጤና ተቋማት፣ ጤና ክብካቤ ባለሙያዎችና የተለያዩ ባለድርሻ አካላት በኢ.ፌ.ዲ.ሪ ጤና ሚኒስቴር እና በኢ.ፌ.ዲ.ሪ መከላከያ ሚኒስቴር በጋራ የተዘጋጀ የምስጋና የእውቅና መርሃ ግብር ተካሄደ፡፡


በፕሮግራሙ ላይ በክብር እንግድነት የተገኙት ጠቅላይ ሚኒስትር ክቡር ዶ/ር አብይ አህመድ ባደረጉት ንግግር የጤና ባለሙያዎችና የጤና ክብካቤ ሰራተኞች እንደ ሰው፣ እንደ ኢትዮጵያዊ እና እንደ ሃኪም ሶስት ማንነትን ተላብሳችሁ ለሰራችሁት ታላቅ ገድል ከፍተኛ ምስጋና ይገባችኋል ብለዋል፡፡

286 ሺህ ዶላር የሚገመት የህክምና ቁሳቁስ ድጋፍ ለቅዱስ ጳውሎስ ሆስፒታል ተደረገ 

Coca-Cola Foundation

ድጋፉን ያደረገው የኮካ ኮላ ኩባንያ የአለም በጎ አድራጎት ክንፍ የሆነው ኮካ ኮላ ፋውንዴሽን ነው፡፡ 


በቅዱስ ጳውሎስ ሆስፒታል ይፋዊ የርክክብ ስነ-ስርአቱ ላይ በክብር እንግድነት የተገኙት የጤና ሚኒስቴር ሚኒስትር ዶ/ር ሊያ ታደሰ የተደረገው ድጋፍ የቅዱስ ጳውሎስ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ለታካሚዎች የጤና አገልግሎት ለመስጠት ያለውን አቅም ለማሳደግ ትልቅ አስተዋጽኦ ይኖረዋል ብለዋል፡፡

በኢትዮጵያ የመጀመሪያው ምግብን መሠረት ያደረገ የአመጋገብ መመሪያ ይፋ ተደረገ 

Nutrition

የጤና ሚኒስቴር፣ የግብርና ሚኒስቴር፣ የትምህርት ሚኒስቴር እና አጋር አካላት በኢትዮጵያ ህብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት አስተባባሪነት በጋራ ያዘጋጁት በኢትዮጵያ የመጀመሪያ የሆነውን ምግብን መሠረት ያደረገ የአመጋገብ መመሪያ (Food-Based Dietary Guidelines (FBDG's) በዛሬው ዕለት ይፋ ሆኗል። 

‘የጤና መረጃ ሥርዓትን ለማሻሻል አጋርነት እና ትብብርን ማጠናከር’ በሚል መሪ ቃል በሀገር አቀፍ ደረጃ የጤና መረጃ ሳምንት ለመጀመሪያ ጊዜ እየተከበረ ነው።

DATA WEEK

በበዓሉ መክፈቻ ላይ ተገኝተው ንግግር ያደረጉት በጤና ሚኒስቴር የሚኒስትር ፅ/ቤት ሀላፊ ዶ/ር ሩት ንጋቱ በጤናው ሴክቴር የሚታየውን የመረጃ ጥራት ተደራሽነት እና አጠቃቀም ጉድለት በመቅረፍ የጤና አግልግሎት ዘርፉን ማሻሻል እና ተደራሽ ማድረግ ዋና የትኩረት አቅጣጫው መሆኑንን ገልፀው የጤናው ዘርፍ የትራንስፎርሜሽን ዕቅድ የትግበራ ዘመን የጤና መረጃ ጥራትን ለማሻሻል የመረጃ አጠቃቀም ባህሪን ለማጎልበት እና መረጃን ዋቢ ያደረገ የውሳኔ አስጣጥ አስራርን ለማስረፅ ከባለድርሻ አካላት ጋር በመሆን ከፍተኛ ጥረት እያደረጉ መሆኑን ተናግረዋል፡፡

በጦርነቱ ጉዳት በደረሰባቸው አካባቢዎች በተደረገ ከሀያ አራት ሚሊየን ብር በላይ የሚገመት የአይን ሕክምና ድጋፍ ከሶስት ሺ በላይ ለሚሆኑ ዜጎች የአይን ቀዶ ጥገና ህክምና መስጠት መቻሉ ተገለጸ፡፡

የአይን ሞራ ግርዶሽ  የነጻ ህክምና

የጤና ሚኒስቴር የበሽታ መከላከል እና መቆጣጠር ዳይሬክቶሬት በአይን ህክምና ዙሪያ ከሚሰሩ መንግስታዊ እና መንግስታዊ ያልሆኑ አጋር ድርጅቶችን በማስተባበር ከሃያ አራት ሚሊየን ብር በላይ  ድጋፍ በማሰባሰብና የህክምና ባለሙያቸው ድጋፍን በማቀናጀት በአፋር እና በአማራ ክልሎች  በጦርነቱ ምክንያት ህክምና ሳያገኙ የቆዩ ከሶስት ሺ በላይ ለሚሆኑ ዜጎች የአይን ሞራ ግርዶሽ  የነጻ ህክምና መስጠት መቻሉን  እና የህክምና ተቋማቱም በመደበኛ አገልግሎታቸው ህክምናውን መስጠት የሚያስችላቸው ስራ መከናወኑን  የጤና ሚኒስትር የበሽታ መከላከል ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር ወ/ሮ ሕይወት ሰሎሞን  አስታወቁ፡፡

በዋቸሞ ዩኒቨርሲቲ የንግስት እሌኒ መሀመድ መታሰቢያ ኮምፕሬሄንሲቭ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል የተለያዩ  አገልግሎቶች ማስጀመሪያ ፕሮግራም ተካሄደ

Inauguration

በፕሮግራሙ ላይ የተገኙት የጤና ሚኒስትር ዶ/ር ሊያ ታደሰ እንደተናገሩት ጥራት ያለው ህክምና ተደራሽነትን ለማሻሻልና  የስፔሻሊቲ እና ሰብ ስፔሻሊቲ ህክምና አገልግሎትን ለመስጠት የተለያዬ የህክምና ቴክኖሎጅዎችን መጠቀም እንደሚያስፈልግ ገልፀው በዛሬው እለትም በዋቻሞ ዩንቨርስቲ የንግስት እሌኒ መሀመድ መታሰቢያ ኮምፕሬሄንሲቭ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ከ40 ሚሊዮን ብር በላይ ወጭ ተደርጎበት የተተከለ የሲቲ ስካን ማሽን መርቀው ስራ አስጀምረዋል።


በተጨማሪም በሆስፒታሉ ለሚገነቡት የኦክስጅን ማምረቻና 450 አልጋ የሚይዝ የእናቶችና ህፃናት ጤና አገልግሎት መስጫ ማዕከል የመሰረተ ድንጋይ አስቀምጠዋል።


የዋና ዋና ከተሞች የድንገተኛ፤ አደጋና ጽኑ ህክምና አገልገሎት ማሻሻያ ፕሮግራም (Major city Emergency and Critical services Improvement Program(MECIP) በተመለከተም የቅድመ ጤና ተቋም የጥሪ ማዕከል አገልግሎትን አስጀምረዋል።

ኢትዮጵያ ከ20 ሚሊዮን በላይ ዜጎቿን የኮቪድ-19 በሽታ መከላከያ ክትባት እንዲከተቡ አድርጋለች!

Dr. Tegene Regassa

የ2ኛ ዙር የኮቪድ-19 ክትባት ዘመቻ አስመልክቶ ጋዜጣዊ መግለጫውን የሰጡት የጤና ሚኒስቴር የህዝብ ግንኙነትና ኮሚኒኬሽን ዳይሬክተር ዶ/ር ተገኔ ረጋሳ ሁለተኛ ዙር የኮቪድ 19 ክትባት ዘመቻ በአገር አቀፍ ደረጃ ከየካቲት 7 ቀን 2014 ዓ.ም ጀምሮ እየተሰጠ እንደሚገኝ የገለጹ ሲሆን በአሁኑ ዘመቻ የተሰጠውን ከ14 ሚሊዮን በላይ ክትባትን ጨምሮ በአጠቃላይ ከ20 ሚሊዮን በላይ ዜጎችን መከተብ መቻሉን አስታውቀዋል፡፡


እንደ ዳይሬክተሩ ገለጻ ከሆነ 17 ሚሊዮን በላይ ሰዎች ሙሉ ለሙሉ ክትባት የወሰዱ ሲሆን ከአንድ መቶ ዘጠና ሁለት ሺህ በላይ የሚሆኑት የማጠናከርያ ክትባቱን (Booster dose) ተከትበዋል፡፡ በጥቅሉ ከ25 ሚሊዮን በላይ ክትባት ጥቅም ላይ እንዲውልም ተደርጓል፡፡  


በዘመቻውም በመጀመርያው ዙር የመከላከያ ክትባቱ ያልተሰጠባቸው የአማራ እና የአፋር ክልሎችን በማካተት ክትባቱን መስጠት መቻሉንም ዳይሬክተሩ አክለው ገልጸዋል፡፡ 

በሶማሌ ክልል በድርቅ የተጎዱ አከባቢዎች ለሚገኙ ጤና ተቋማት አገልግሎት የሚውል ሰላሳ አንድ ሚሊዮን ብር የሚገመት የተለያዩ መድሀኒቶች፣ የተመጣጠነ ምግብ እና የህክምና ቁሳቁሶች ድጋፍ ተደርጓል። 

donation

በጤና ሚኒስትር ዴኤታ ወ/ሮ ሰሀረላ አብዱላሂ የተመራ ከጤና ሚኒስቴር፣ የኢትዮጵያ ህብረተሰብ ጤና ኢንሰቲትዩት እና የኢትዮጵያ መድሀኒት አቅራቢ አገልግሎት የተውጣጣ ከፍተኛ የስራ ሃላፊዎች ቡድን በሶማሌ ክልል በድርቅ የተጎዱ አከባቢዎች ለሚገኙ ስድስት የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል እና ስድስት ጤና ጣቢያዎች አገልግሎት የሚውል የመድሀኒት፣ የተመጣጠነ ምግብ እና የህክምና ቁሳቁሶችን  አስረክቧል። 


ሰላሳ አንድ ሚሊዮን ብር የሚገመት መድሀኒት፣ የተመጣጠነ ምግብ እና የህክምና ቁሳቁሶች በሁለት ዙር በክልሉ ጤና ቢሮ በኩል ወደ ጤና ተቋማት የሚደርስ ርክክብ ተደርጓል። 


በቀጣይም በድርቅ ለተጎዱ የኦሮሚያ፣ ደቡብ ብ/ብ/ህ/ክ እና ደቡብ ምእራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል የምግብና መድሀኒት አቅርቦት እንደሚቀጥል ወ/ሮ ሰሀረላ ገልጸዋል።