በሶማሌ ክልል በድርቅ የተጎዱ አከባቢዎች ለሚገኙ ጤና ተቋማት አገልግሎት የሚውል ሰላሳ አንድ ሚሊዮን ብር የሚገመት የተለያዩ መድሀኒቶች፣ የተመጣጠነ ምግብ እና የህክምና ቁሳቁሶች ድጋፍ ተደርጓል። 

  • Time to read less than 1 minute
donation

በጤና ሚኒስትር ዴኤታ ወ/ሮ ሰሀረላ አብዱላሂ የተመራ ከጤና ሚኒስቴር፣ የኢትዮጵያ ህብረተሰብ ጤና ኢንሰቲትዩት እና የኢትዮጵያ መድሀኒት አቅራቢ አገልግሎት የተውጣጣ ከፍተኛ የስራ ሃላፊዎች ቡድን በሶማሌ ክልል በድርቅ የተጎዱ አከባቢዎች ለሚገኙ ስድስት የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል እና ስድስት ጤና ጣቢያዎች አገልግሎት የሚውል የመድሀኒት፣ የተመጣጠነ ምግብ እና የህክምና ቁሳቁሶችን  አስረክቧል። 


ሰላሳ አንድ ሚሊዮን ብር የሚገመት መድሀኒት፣ የተመጣጠነ ምግብ እና የህክምና ቁሳቁሶች በሁለት ዙር በክልሉ ጤና ቢሮ በኩል ወደ ጤና ተቋማት የሚደርስ ርክክብ ተደርጓል። 


በቀጣይም በድርቅ ለተጎዱ የኦሮሚያ፣ ደቡብ ብ/ብ/ህ/ክ እና ደቡብ ምእራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል የምግብና መድሀኒት አቅርቦት እንደሚቀጥል ወ/ሮ ሰሀረላ ገልጸዋል።