የኮሪያ መንግስት በኮፍ /KoFIH / ግብረሰናይ ድርጅት እና ኤክዚም ባንክ በኩል ለጤና ሚኒስቴር የኮቪድ 19 የዲያግኖስቲክ ላብራቶሪ ቁሳቁሶችን ድጋፍ አደረገ

The Korean government

በርክክብ ሥነ ሥርዓቱ ላይ የተገኙ የጤና ሚኒስቴር  ሚኒስትር ዶ/ር ሊያ ታደሰ የኮሪያ መንግሥት በተለያዩ ሥራዎች የጤና ሴክተሩን እንደሚያግዝ ተናግረው ይበልጥ በእናቶችና ህፃናት ጤና፣ በጤና መድህን አገልግሎት፣ የህክምና ባለሙያዎች ስልጠና፣ የህክምና ቁሳቁስ ጥገና እና ኮቪድ-19ን መከላከልና መቆጣጠር እንዲሁም የፅኑ ህሙማን ህክምና መሣሪያዎች ላይ ያደረጉትን ድጋፍ  አንስተዋል፡፡ 


የተደረገው ድጋፍ የኮቪድ-19ን ለመከላከልና ለመቆጣጠር  ጠቀሜታ  የጎላ  እንደሆነ ዶ/ር ሊያ ታደሰ  የተናገሩ ሲሆን ይህ ድጋፍ የሁለቱ ሃገራት ጥብቅ ግንኙነት ያሳያል ብለዋል፡፡


የኮፍ /KoFIH / ግብረ ሰናይ ድርጅት ፕሬዘዳንት ኘ/ር ቺያግ ዩፐ ኪም የኢትዮጵያ እና የደቡብ ኮሪያ ግንኙነት ረጅም አመታት ያስመዘገበ መሆኑን አውስተው የኮቪድ-19 የዲያግኖስቲክ ላብራቶሪ ቁሳቁሶችን ድጋፍ በተጨማሪ የመጀመሪያ ደረጃ ጤና ሥርዓት ማጠናከር ላይ በትኩረት  እንደሚሠሩ ተናግረዋል፡፡

በክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎት በጋምቤላ ክልል የአቅመ ደካሞችን ቤት የማደስ ስራ ተጀመረ 

Dr. Lia Tadesse

በ2014 በጀት ዓመት በጤና ሚኒስቴር አስተባ ባሪነት ተጠሪ ተቋማትን ባከተተ መንገድ የተለያዩ የክረምት በጎፍቃድ ስራዎች እየተከናወኑ ይገኛል።


 የጤና ሚኒስትር ዶ/ር ሊያ ታደሰ በክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎት የአቅመ ደካሞችን ቤት የማደስ ማስጀመሪያ መርኃ ግብር ዛሬ በጋምቤላ ከተማ፣ የአቅመ ደካማ ቤቶች እድሳትን አስጀመሩ። በዚህም የ 5 አቅመ ደካሞች ቤት ሙሉ በሙሉ የሚታደስ ይሆናል።


በክልሉ የአቅመ ደካማ ወገኖችንን ቤት ከማደስ ፕሮግራም ማስጀመር በተጨማሪ  የጋምቤላ ከተማ የመጀመሪያ ደረጃ  ሆስፒታል  የድንገተኛ ህክምና አገልግሎት አሰጣጥ፣ በክልሉ የሚገነባው ሪጅናል ላብራቶሪ ግንባታ ሒደት፣ እንዲሁም አሻራችን ለትውልዳችን በሚል መሪ መልክት  በጋምቤላ ከተማ ጤና ጣቢያ የችግኝ ተከላ ተካሒዷል። 


 በመርሀ ግብሩም በክልሉ በዝቅተኛ ገቢ ከሚተዳደሩ የአቅመ ደካማ ልጆች ለ400 ተማሪዎች የትምህርት ቁሳቁስና ድጋፍ ተደርጓል። 

የእናት ጡት ወተት የህይወት ምግብ!

Dr. MESSERET ZELALEM

“ምቹ ሁኔታ ለሚያጠቡ እናቶች፤ እናስተምር፤ እንደግፍ!!” በሚል መሪ ቃል የዘንድሮው የጡት ማጥባት ሣምንት በዓለም ለሰላሳኛ በሀገራችን ደግሞ ለአስራ አራተኛ ጊዜ እየተከበረ ነው፡፡

የሥርዓተ ምግብ ችግሮች በዓለም ላይ በየዓመቱ ወደ አምስት ሚሊዮን ሕፃናት ህመምና ሞት ምክንያት ነው ያሉት የጤና ሚኒስቴር የእናቶች ህፃናት እና የስርዓት ምግብ ዳይሬክተር ዶ/ር መሰረት ዘላለም ከፅንስ ጀምሮ እስከ ሁለት ዓመት ዕድሜ ባለው ጊዜ ማስተካከል ካልተቻለ መቀንጨር እና ሌሎች የምግብ አለመመጣጠን ችግሮች ሊከሰት እና በቀጣዩ የእድሜ ክልል ከትውልድ ወደ ትውልድ ሊተላለፍ የሚችል አመጋገብ ችግር ይሆናል ብለዋል።

ኦሀዮ ስቴት ዩኒቨርሲቲ ግሎባል ዋን ሄልዝ ፕሮግራም  በሰሜኑ ክፍል በነበረው ጦረነት ለተጎዱ የጤና ተቋማት ድጋፍ አደረገ

Ohio State University

በዛሬው እለት የተደረገው ድጋፍ 9 ሚሊዮን ብር የሚያወጡ የላብራቶሪ እቃዎች መሆናቸው ማወቅ የተቻለ ሲሆኑ ድጋፉ የተደረገው በአማራ እና በአፋር በክልል ለሚገኙ ስድስት ሆስፒታሎች ሲሆን በስድስቱ ሆስፒታሎች ውስጥ ላሉ የላብራቶሪ ክፍሎችን መልሶ ለማደረጃት የሚረዳ ድጋፍ ነው፡፡


በርክክብ ስነስርዓቱ ላይ ንግግር ያደረጉት የጤና ሚኒስትር ዶክተር ሊያ ታደሰ እንዳሉት በአገራቱ የነበረው ጦርነት የጤና ተቋማትን ማውደሙን ተከትሎ መልሶ ለማቋቋም በተደረገው ርብርብ ሁሉም ሆስፒታሎች ወደ ስራ እንዲገቡ መደረጉን አንስተዋል፡፡ ኦሀዮ ስቴት ዩኒቨርሲቲ ግሎባል ዋን  ሄልዝ ፕሮግራም ለዚህ ችግር ትኩረት በመስጠት  የሆስፒታሎችን ላብራቶሪዎች ሙሉ ለሙሉ ለመደገፍ መቻሉን ዶክተር ሊያ የተናገሩ ሲሆን በቴክኒክም የማጠናከር ስራ እየሰራ መሆኑንም ነው የገለጹት፡፡ 

የግሎባል ፈንድ አፈጻጸም እና ትግበራ በተመለከተ ከሲውዘርላንድ ከመጡ ከፍተኛ የተቋሙ አባላት ጋር ውይይት ተደረገ

Global Fund

ሲውዘርላንድ ጄኔቭ ከሚገኘዉ የግሎባል ፈንድ ዋና መስሪያቤት የመጣው ከፍተኛ የአመራርና የባለሙያዎች ቡድን ጋር በደተረገው ውይይት ላይ የሃይ ኢምፓክት አፍሪካ ሄድ ኦፍ ዲፓርትመንት እና የዴሊጌሽኑ መሪ የሆኑት ሊንደን ሞሪሰን እንዳሉት ኢትዮጵያ የተላያዩ ችግሮች ያጋጠሟት ቢሆንም በግሎባል ፈንድ ድጋፍ የሚደረግላቸዉ የጤና ፕሮግራሞች አፈጻጸም ግን ጥሩ በመሆኑ ደስተኞች መሆናቸውን ተናግረዋል፡፡


በግሎባል ፈንድ ስር የሚከወኑ ፕሮግራሞችን እና የኮቪድ መከላከል ስራዎች መልካም ውጤት ያስገኙ መሆናቸው የገለጹት የጤና ሚኒስቴር ዶ/ር ሊያ ታደሰ ናቸው፡፡ የውጭ ምንዛሬ አለመረጋጋት እና ግጭት የግሎባል ፈንድ አፈጻፀም እና ትግበራ ላይ ያጋጠሙ ችግሮች እንደሆኑ ዶ/ር ሊያ ተናግረዋል፡፡ ያጋጠሙ የአቅርቦት ችግሮችን መቅረፍ ይገባል ያሉት ዶ/ር ሊያ፣ በግሎባል ፈንድ አፈጻጸም እና ትግበራ ላይ አጋር ድርጅቶች ያደረጉትን ተሳትፎ አድንቀዋል፡፡

በክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎት የአቅመ ደካሞችን ቤት የማደስ ስራ ተጀመረ 

Dr. Lia Tadesse

የጤና ሚኒስቴር እና ተጠሪ ተቋማት በክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎት የአቅመ ደካሞችን ቤት የማደስ ማስጀመሪያ መርኃ ግብር  ዛሬ በልደታ ክፍለ ከተማ፣ ወረዳ 5 የጤና ሚኒስትር ዶክተር ሊያ ታደሰ አስጀምረዋል።


መርኃ ግብሩ ላይ የጤና ሚኒስትር ዶክተር ሊያ ታደሰ፣ ሚኒስትር ዴኤታ ዶ/ር አየለ ተሾመ እና የተጠሪ ተቋማት የስራ ኃላፊዎች እና ሌሎች የሥራ ኃላፊዎችና ሰራተኞች ተገኝተዋል።


ጤና ሚኒስቴርና ከተጠሪ ተቋማት ጋር በመሆን በዘንድሮው መርሐግብር 12 አቅመ ደካሞችን በአዲስ አበባ እና 5 ቤቶችን በክልሎች የሚገነቡ ሲሆን ይህም የእርስ በእርስ የመደጋገፍ ባህልን የሚያዳብርና ለመጪው ትውልድም መልካም እሴትን የሚያሸጋግር ታላቅ በጎ ስራ ነው ብለዋል ሚኒስትር ዶ/ር ሊያ ታደሰ፡፡

ለትግራይ ክልል በአለም አቀፍ ድርጅቶች በኩል አስፈላጊ የህክምና መድሃኒቶችን የማድረሱ እንቅስቃሴ እንደቀጠለ ነው

 supplies

የኢትዮጵያ መንግስት ከሚሰራቸው ቀዳሚ ተግበራት መካከል የጤና አገልግትን ለሁሉም ዜጎች ማድረስ አንደኛው ሲሆን በኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ ህገ መንግስትም እያንዳንዱ ዜጋ የጤና አገልግሎት የማግኘት ጉዳይን በግልጽ ተጠቅሷል፡፡


ስለሆነም ዜጎች  የጤና አገልግሎት በፍትኃዊነት የማግኘት መብት ተግባራዊ ለማድረግ የሚያስችሉ የፖሊሲ አቅጣጫዎች በኢፊዲሪ የጤና ፖሊሲ ተካተዋል፡፡


ከዚህ አኳያ በአገራችን በተከሰቱ ግጭቶች ምክንያት ዜጎች የጤና አገልግሎቶችን የማግኘት ሰብዓዊና  ህገ መንግስታዊ መብቶች እንዳይስተጓጎሉ የኢትዮጵያ መንግስት በተለያዩ ጊዜያት ከአለም አቀፍ አጋር ድርጅቶች ጋር በመሆን ለጤና አገልግሎት አስላፈጊ የሆኑ ድጋፎችን የማድረስ ተግበራትን  አከናውኗል፣ እያከናወነም ይገኛል፡፡

የጤና ሚኒስቴር ''አሻራችን ለትውልዳችን፣ አረንጓዴ ተክላችን ለጤንነታችን!" በሚል መሪ ቃል የችግኝ ተከላ ማስጀመሪያ በኢትዮጵያ የአካል ድጋፍ አገልግሎት ማዕከል ተከናወነ።

Dr. Lia Tadesse

በዛሬው ዕለት የችግኝ ተከላ ማስጀመሪያ መርሐ ግብር በኢትዮጵያ የአካል ድጋፍ አገልግሎት (በገፈርሳ የአዕምሮ ህሙማን ማገገሚያ ማዕከል) የተከናወነ ሲሆን በ2014 ዓ.ም ክረምት ወራት የጤና ሚኒስቴርና ተጠሪ ተቋማት  ከ50 ሺ በላይ ችግኞችን ለመትከል ወደ ተግባር መግባቱን የጤና ሚኒሰቴር ሚኒስትር ዶ/ር ሊያ ታደሰ ተናግረዋል።


በኢትዮጵያ የአካል ድጋፍ አገልግሎት (በገፈርሳ የአዕምሮ ህሙማን ማገገሚያ ማዕከል 20  ሺህ ለምግብነት የሚውሉ ችግኞች የመትከሉ መርሀ ግብር የተከናወነ ሲሆን በተጨማሪም በማእከሉ የተከናወኑ የልማት እና የማስፋፊያ ስራዎች የወተት ልማትን ጨምሮ የከተማ ግብርናን የመተግበር ስራ እንዲሁም የህክምና አገልግሎት አሰጣጥ ተጎብኝተዋል። ይህም ተግባር በማዕከሉ ያለውን የምግብ አቅርቦት በራስ አቅም ለመሸፈን ያስችላል ተብለዋል።

የሚሊኒየም ኮቪድ ህክምና እና ድንገተኛ ምላሽ ማዕከል የምስጋና እና የማስረከብ ፕሮግራም ተከናወነ

የሚሊኒየም ኮቪድ ህክምና እና ድንገተኛ ምላሽ ማዕከል

የጤና ሚኒስቴር ላለፉት ሁለት ዓመታት የኮቪድ የህክምና እና የድንገተኛ ምላሽ ማዕከል ሆኖ ሲያገለግል የቆየውን አዲስ ፓርክ /የሚሊኒየም አዳራሽ/ ከምስጋና ጋር ለሜድሮክ ኢንቨስትመንት ግሩፕ አስረከበ።


የጤና ሚኒሰቴር ሚኒስትር ዶ/ር ሊያ ታደሰ ማዕከሉን ለሜድሮክ ኢንቨስትመንት ግሩፕ ባስረከቡበት ወቅት እንደገለፁት ባለፉት ሁለት ዓመታት የኮቪድ ወረርሽኝን ለመከላከል ብዙ ውጣ ውረዶች ማለፋቸውን ጠቅሰው ዛሬም ኮቪድ እያስከተለ ያለው ችግር ባይቆምም ለዚህ ዕለት በመብቃታችንና የሚሊኒየም የህክምና ማዕከልን መልሰን ማስረከብ በመቻላችን ደስተኞች ነን ብለዋል።

የቤተሠብ እቅድ አገልግሎትን ለማስፋፋት የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት የድርሻቸውን ሀላፊነት እንደሚወጡ ገለፁ። 

House of Representatives

ይህ የተገለፀው የጤና ሚኒስቴር በቤተሠብ እቅድ አገልግሎት ተደራሽነት፣ ስኬት እና ክፍተት በተመለከተ ለህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት ባደረገው የግንዛቤ መስጨበጫ መድረክ ላይ ነው። በመድረኩ ተገኝተው ንግግር ያደረጉት የጤና ሚኒስትር ዴኤታ ዶክተር ደረጀ ድጉማ እንዳሉት የቤተሠብ እቅድ አገልግሎት መስጠት የሴቶች እና ህጻናት ህይወት ለመታደግ ዋነኛው አቅጣጫ መሆኑን ጥናቶች እንደሚያመለክቱ ጠቅሰው ይህን አገልግሎት ተደራሽ ማድረግ ላይ ትኩረት ተሠጥቶ ሊሠራ እንደሚገባ ገልጸዋል።


ባለፉት አመታት በቤተሠብ እቅድ አገልግሎት የተሠሩ ሥራዎች እና የተገኙ መሻሻሎች እንደተጠበቁ ሆነው አሁንም 22 በመቶ የሚሆኑ በለትዳር ሴቶች አገልግሎቱን ለማግኘት ቢፈልጉም ተደራሽ ማድረግ አለመቻሉን የገለጹት ሚኒስትር ድኤታው ይህም በበጀት አመቱ የገንዘብ እጥረት በማጋጠሙ ምክንያት መሆኑም አስረድተዋል።