የመሀል ሜዳ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል መደበኛ የሕክምና አገልግሎት እየሰጠ ይገኛል።" የሆስፒታሉ ሥራ አስኪያጅ አቶ ወርቅነህ ዘዉዴ 

Mehal Meda

በአሸባሪውና ዘራፊው ቡድን የሕክምና አገልግሎት ያቋረጠው የመሀል ሜዳ ሆስፒታል በዳግማዊ ሚኒልክ ሆስፒታልና በአካባቢው ማህበረሰብ በተደረገለት ድጋፍ የህክምና አገልግሎት መስጠት መጀመሩን የሆስፒታሉ ሥራ አስኪያጅ አቶ ወርቅነህ ዘዉዴ ተናገሩ።


ሆስፒታሉ በተደረገለት የህክምና መገልገያ መሳሪያዎችና የመድኃኒት አቅርቦት ድጋፍ የእናቶችና የህፃናት ጤና አገልግሎት፣ የድንተኛና ጽኑ ሕሙማን አገልግሎት የተመላላሽ ህክምና አገልግሎት በየእለቱ በአማካይ ከ 150 እስከ 200 ታካሚዎች አገልግሎት እየተሰጠ እንደሚገኝ ገልጸው ሙሉ ለሙሉ ሆስፒታሉን ወደ ስራ ለመመለስ ተጨማሪ ድጋፎች እንደሚያስፈልጉ ሥራ አስኪያጁ ተናግረዋል።


በሆስፒተሉ ሲገለገሉ ያገኘናቸው ወ/ሮ አስካለ ገዛኸኝ እና አቶ በልዩ ካሳዬ ተመላላሽ ህክምና ክትትላቸው በመቋረጡ ከፍተኛ ስጋት እንዳሳደረባቸው ገልጸው ሆስፒታሉ አገልግሎት ጀምሮ በማየታቸው መደሰታቸውን ተናግረዋል።

ጤና ሚኒስቴር ለአማራ ክልል ለወደሙ የጤና ተቋማት  አጋር አካላትን በማስተባበር ከ21 ሚሊየን ብር በላይ  የሚያወጡ የህክክምና ግብአቶችን፣ መድሀኒቶችን፣ አንቡላንሶችን እና የጥሬ ገንዘብ ድጋፍ አስረከበ። 

donation

የጤናማ እናትነት ወር በደሴ ከተማ በተከበረበት ስነስርአት ጤና ሚኒስቴር አጋር አካላትን በማስተባበር ለእናቶች እና ህጻናት ጤና ከፍተኛ እገዛ ማድረግ የሚችሉ ከ21 ሚሊየን ብር በላይ የሚያወጡ የህክምና ግብአቶችን፣ መድሀኒቶችን፣ ሁለት አንቡላንሶችን እና ጥሬ ገንዘብ ድጋፍ አበርክቷል። 


የጤና ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴኤታ ዶ/ር ደረጀ ዱጉማ በርክክቡ ወቅት እንደተናገሩት ወራሪው ሀይል ተቋሞቻችንን ቢያወድምም ጠንካራ መንፈሳችንን እና ህብረታችንን ከቶ ሊሰብር አይቻለውምና ከቀድሞ በበለጠ እጅ ለእጅ ያተያይዘን ተቋሞቻችንን እንገነባለን ሲሉ ተናግረዋል።

ደሴ ኮምፕርሄንሲቭ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ወደ አገልግሎት አሰጣጥ በመመለሱ መደሰታቸውን ተገልጋዮች ገለፁ

Community

በጦርነቱ ምክንያት ከረጅም ጊዜ ቆይታ በኋላ የህክምና አገልግሎት መስጠት በጀመረው የደሴ ኮምፕርሄንሲቭ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ግልጋሎት በማግኘታቸው መደሰታቸውን ነዋሪዎች ገለፁ።


በሆስፒታሉ ሲገለገሉ ያገኘናቸው ወ/ሮ መሬሞ ሙሄ እና አቶ አበበ አብረሀም እንደገለፁት የሆስፒታሉ በሮች ተከፍተው ነጭ ገዋን የለበሱ የጤና ባለሙያዎች በፈገግታ ታካሚዎችን ሲያስተናግዱ በማየታቸው ተደስተዋል።


ህዳር 25/ 2014 ዓ ም በሆስፒታሉ እንድትገኝ ከሀኪሟ ቀጠሮ ተሰጥቷት እንደነበርና በነበረው ጦርነት ምክንያት እንዳላቀረበች የተናገራቸው መሬሞ ያ የስቃይ ጊዜ አልፎ ዛሬ ወደ ሆስፒታሉ በመቅረብ ተመርምራ መድሀኒት ሊታዘዝላት በመቻሉ ከጭንቀት እንደገላገላት መስክራለች።


እህቴን ለማሳከም መጥቼ ተገቢውን አገልግሎት አግኝቼ የራጅ ምርመራ ውጤት እየጠበቅን ነው ያለው አበበ በበኩሉ ለዚህ ብርሀናማ ቀን በመብቃታችን ፈጣሪንና መንግስትን አመሰግናለሁ ብሏል።

"የእናቶችን ሞት ለማስቀረት ሁሉም አካላት ቀዳሚ አጀንዳ በማድረግ ሊሰሩ ይገባል!" ዶ/ር ደረጀ ዱጉማ የጤና ሚኒስትር ዴኤታ

Dr. Dereje Duguma

"በማንኛውም ሁኔታ ከወሊድ በሁዋላ በደም መፍሰስ ምክንያት የሚከሰተውን የእናቶች ሞት እጅ ለእጅ ተያይዘን እንግታ" በሚል መሪ ቃለ በአማራ ክልላዊ መንግስት ደሴ ከተማ በተከበረበት ወቅት የጤና ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴኤታ ዶክተር ደረጀ ዱጉማ እንደተናገሩት በሀገራችን በቀን ከሰላሳ በላይ እናቶች ከወሊድ ጋር በተያያዘ ህይወታቸውን እንደሚያጡ ተናግረው እንደ ደሴ ባሉ በህውሀት አሸባሪ ቡድን የጦርነት ጥቃት እና ዘረፋ በተከሰተባቸው አካባቢዎች ችግሩ ሊከፋ እንደሚችል በመረዳት ሁሉም አካላት በከፍተኛ ትኩረት ሊሰሩ እንደሚገባ አስረድተዋል፡፡

 
አሸባሪው ብድን የጤና ተቋማቱን ቢያወድሙና ቢዘርፉም ጠንካራ መንፈሳችንን ግን ሊነኩት አይቻላቸውምና ደግመን ተረባርበን በመገንባት ለእናቶችና ለሌሎችም የጤና አገልግሎቶችን በተሻለ እናቀርባለን ብለዋል፡፡  

የኮቪድ 19ን ለመከላከልና ለመቆጣጠር እንዲሁም የወደሙ ተቋማትን መልሶ ለማቋቋም የሚያግዝ ሰው ሰራሽ መተንፈሻ መሳሪያ ድጋፍ ርክክብ ተደረገ

Delivery

ግምታቸው 30 ሚሊዮን ብር የሚሆን 100 ሰው ሰራሽ መተንፈሻ መሳሪያዎች የኮቪድ 19ን ለመከላከልና ለመቆጣጠር እንዲሁም የወደሙ ተቋማትን መልሶ ለማቋቋም የሚያግዝ ሰው ሰራሽ መተንፈሻ መሳሪያ ድጋፍ ለጤና ሚኒስቴር ተደርጓል፡፡

 
ድጋፉን ለጤና ሚኒስቴር ሚኒስትር ዶ/ር ሊያ ታደሰ  ያስረከቡት የሞደርን ኢ.ቲ.ኤች አውት ሶርስ ፒ.ኤል.ሲ ተወካይ የሆኑት አቶ ታዲዮስ ተፈራ፤ ድጋፉ የተደረገው በኮቪድ የተጠቁ ዜጎችን ለመርዳት ታስቦ መሆኑን ገልጸው ድጋፋቸው የሚቀጥል መሆኑን ተናግረዋል፡፡

 
 የጤና ሚኒስቴር ሚኒስትር ዶክተር ሊያ ታደሰ ፣ ድጋፉን ያደረጉትን ድርጅቶች አመስግነው፤ መሳሪያዎቹ በጽኑ ህሙማን ማገገሚያ የሚገኙ ታካሚዎችን ለመርዳት ከፍተኛ እገዛ እንደሚያደርጉ ገልጸው ድጋፋቸውን አጠናክረው እንዲቀጥሉ ጠይቀዋል።

"እናቶች በጤና ተቋማት በሰለጠኑ ባለሙያዎች እንዲወልዱ ሁሉም የድርሻውን መወጣት አለበት።"  ዶ/ር ደረጀ ዱጉማ የጤና ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴኤታ

Dr. Dereje Duguma

የጤናማ እናትነት ወር "በማንኛውም ሁኔታ ከወሊድ በኋላ በደም መፍሰስ ምክንያት የሚከሰተውን የእናቶችን ሞት እጅ ለእጅ ተያይዘን እንግታ" በሚል መሪ ቃል በአለም ለ35ኛ በሀገራችን ደግሞ ለ16ኛ ጊዜ በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ጤና ቢሮ አስተባባሪነት በአበበች ጎበና የእናቶችና ህፃናት ሆስፒታል ተከብሯል፡፡ 


የጤና ሚኒስቴር ዴኤታ ዶ/ር ደረጀ ዱጉማ በዓሉን አስመልክተው ባደረጉት ንግግር በሀገራችን ከእናቶች ሞት ጋር ተያይዞ በተደረገው ጥናት በዓመት ከሚሞቱት እናቶች በተለይ 50 በመቶ የሚሆኑት ከደም መፍሰስ ጋር በተያያዘ ምክንያት መሆኑን ገልፀው እናቶች በጤና ተቋማት በሰለጠኑ ባለሙያዎች እንዲወልዱ ሁሉም የድርሻውን መወጣት አለበት ብለዋል፡፡ ለዚህም የሃይማኖት አባቶች፣ የሚዲያ ባለሙያዎች፣ የኪነጥበብ ሰዎች፣ በየደረጃው ያሉ አመራሮች፣ የጤና ባለሙያዎችና ሌሎች ባለድርሻ አካላት ግንዛቤ በመፍጠር እናቶች በህክምና ተቋም እንዲወልዱ እንዲያበረታቱ አሳስበዋል፡፡

በጦርነት እና በተለያዩ ግጭቶች ምክንያት ጉዳት ለደረሰባቸው ዜጎች የስነ አዕምሮ እና የስነ ልቦና ህክምና  ምላሽ ለመስጠት የሚያስችል በጤና ሚኒስቴርና በሴቶችና ማህበራዊ ጉዳዮች ሚኒስቴር የተዘጋጀ የዘርፈ ብዙ ምላሽ እቅድ ይፋ ተደረገ

ministers

በተለያዩ ክልሎች በጦርነት እና በተፈጠሩ ግጭቶች ለተፈናቀሉና ጉዳት ለደረሰባቸው ዜጎች የተቀናጀ  የስነ አዕምሮ እና የስነ ልቦና ህክምና ምላሽ  በመስጠት እየተደረገ ያለውን ድጋፍ ይበልጥ ለማጠናከርና ፈጣን ለማድረግ የጤና ሚኒስቴር እና የሴቶችና  ማህበራዊ ጉዳዮች ሚኒስቴር በጋራ ያዘጋጁት እቅድ ለባለድርሻ አካላት በኢትዮጵያ የህረተሰብ ጤና ኢንስትቲዩት የህብረተሰብ ጤና አደጋዎች የመልሶ ማቋቋምና ሪዚሊየንስ ዳይሬክተር በሆኑት በዶ/ር ያረጋል ፉፋ ቀርቦ ውይይት ተደርጎበታል።


በቅንጅታዊ  ርብርቡ የስነ አዕምሮ ፣  የስነ ልቦና እና የማህበራዊ ስራዎች እንዲሁም ለተለያዩ ባለድርሻ አካላት ግንዛቤ የመፍጠር ተግባራት እንደሚከናወኑ በእቅዱ የተካተቱ ዝርዝር አላማዎች ያሳያሉ፡፡ 

በ2030 እ.ኤ.አ. በሀገር አቀፍ ደረጃ የቤተሰብ ዕቅድ አገልግሎትን ለማሳካት የሚያግዝ የቃል መግቢያ ሰነድ ይፋ ተደረገ 

family planning

ይህ የቤተሰብ እቅድ 2030 የቃል መግቢያ ሰነድ አለም አቀፋዊ ሲሆን 69 ሀገራት የሚሳተፉበት ነው። 


በመድረኩ ላይ የተገኙት የጤና ሚኒስትር ዶ/ር ሊያ ታደሰ እንደተናገሩት በ2030እ.ኤ.አ የቤተሰብ እቅድ አገልግሎትን በሀገርአቀፍ ደረጃ ለማሳካት በምንገባው  ቃል መሰረት የእናቶችና የህፃናትን ጤና ብሎም የአፍላ ወጣቶችንና የወጣቶችን ስነ-ተዋልዶ ጤና  በማሻሻል የተሻለ ጤናማ ዜጋ በመፍጠሩ ረገድ መንግስት ሰፊ ስራ መስራት እንዳለበት ገልጸዋል:: የሁሉንም ተሳትፎ ባካተተ መልኩ የተዘጋጁት የጤናዉ ፖሊሲ ስትራቴጂዎችና  የማስፈጸሚያ ሰነዶችን ወደ ተግባር የመለወጥ ስራ ላይ ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በቅንጅት መስራት እንደሚያሰፈልግና  በገባነው ስምምነት መሠረት ያሉብንን ተደራራቢ ጫናዎችን በመቋቋም ብሎም በጋራ በጥምረት በመስራት ጤናማ ትውልድን ለመፍጠር እና ጤናማ ሀገርን ለመገንባት ይህ የቃል መግቢያ ሰነድ መዘጋጀቱንና ይፋ መደረጉን ተናግረዋል:: 

ጥራት ያለውን የጤና አገልግሎት ተደራሽ ለማድረግ ባለድርሻ አካላት አጋርነታቸውን እንዲያጠናክሩ ተጠየቀ

universal health coverage day

ሁሉን አቀፍ የጤና አገልግሎት ተደራሽነት ቀን /INTERNATIONAL UNIVERSAL HEALTH COVERAGE COMMEMORATION DAY/ “የጤና ኢንቨስትመንት ለሁሉም" /INVEST IN HEALTH SYSTEMS FOR ALL/ በሚል መሪ ቃል በዓለም ዓቀፍ ደረጃ እየተከበረ ነው፡፡ 


ሁሉን አቀፍ የጤና አገልግሎት ተደራሽነት ቀን ሲከበር አጋር አካላት አጋርነታቸውን በመቀጠል በጦርነት የወደሙ ጤና ተቋማትን መልሶ ለማቋቋምና ለአገልግሎት ብቁ ለማድረግ እንዲሰሩ ጠይቀዋል፡፡

ከፍተኛ ውድመት የደረሰባቸውን የጤና ተቋማት ለማቋቋምና መልሶ ስራ ለማስጀመር እንዲቻል ከጤና ሚኒስቴር የቀረበ  ሁሉን-አቀፍ የድጋፍ ጥሪ!

Health Facility

አሸባሪው የጥፋት ቡድን ህወሓት በወረራ ይዟቸው በነበሩ አካባቢዎች ካደረሰው ሰብዓዊና ሞራላዊ ጥፋት በተጨማሪ  ህዝብ የሚገለገልባቸውን የጤና አገልግሎት ሰጪ ተቀቋማት፤ የህክምና ግብዓት ማከማቻ ተቋማትን እና ሌሎች ማህበራዊ ተቋማት አውድሟል፡፡ የህክምና መሳርያዎችን እና ሌሎች ግብዓቶችንም ጭኖ በመውሰዱ ዝርፍያ እና ጉዳት ፈጽሟል፡፡

 
በጤና ተቋማት ላይ የደረሰው ወድመት በተለይ ድጋፍ ለሚሹ ዜጎች የመሰረታዊ እና ድንገተኛ ህክምና አግልግሎት አሰጣጥ በእጅጉ አስተጓጉሏል። እስካሁን በደረስንበት መረጃ ከ2700 በላይ የሚሆኑ የጤና ተቋማት አገልግሎት የማይሰጡ ሲሆን በአሁን ወቅት በመንግስት ተደራሽ ያልሆኑ አከባቢዎች ሲካተቱ ዉድመት የደረሰባቸዉ ቁጥር ከዚህ እንደሚያሻቅብ ይጠበቃል።