የጡት ካንሰር ግንዛቤ ወር የክብርት ፕሬዚደንት መልዕክት

HE the President

የጥቅምት ወር የጡት ካንሰር ግንዛቤ ወር ነው። የጡት ካንሰር ሴቶችን በከፍተኛ  ደረጃ ያጠቃል። በአገራችን ታካሚዎች ወደ ጤና ተቋም የሚሄዱት ዘግይተው ነው። የሚታዩ ምልክቶችን በጊዜ ለመለየት ቅድመ ምርመራ እንዲደረግ የሚመለከታቸው ሁሉ በቂ ግንዛቤ ሊይዙ ይገባል። ይህ ባለመሆኑ ብዙዎችን አጥተናል።


ከአገራችን የተለያዩ ክፍሎች ለጨረርና ለኪሞ ሕክምና የሚመጡ ሴት ወገኖቻችን መጠለያ ቦታ ስለሌላቸው ለተጨማሪ ችግር ይጋለጣሉ። ችግሩን ለመቅረፍ ለእነዚህ ሕሙማን ማረፍያ ቦታ በማዘገጀት፣  ወደ ሆስፒታል በማመላለስ፣ መድሃኒት ግዢ ላይ በመደገፍ ወዘተ . . . ከሚሠሩ ድርጅቶች መካከል "ፒንክ ሃውዝ" የተባለውን በቅርብ ጎብኝቻለሁ። ይህንንና ተመሳሳይ ተቋሟችን በመደገፍ ሴቶች በጊዜ ከተደረሰበት ሊታከም በሚችል በሽታ እንዳይጎዱ እናድርግ።

"የጤና መድህን አባላትን ቁጥር በማሳደግ የዜጎችን ተጠቃሚነት የማረጋገጡ ስራ ተጠናክሮ ሊቀጥል ይገባል" የጤና ሚኒስቴር ሚኒስትር ዶ/ር ሊያ ታደሠ

lia

አገር አቀፍ የጤና መድህን አገልግሎት የ2013 በጀት ዓመት ዕቅድ አፈጻጸምና የ2014 ዓ.ም ዕቅድ ግምገማ ጉባኤ ማጠቃለያ ላይ ተገኝተው የስራ አቅጣጫ የሰጡት የጤና ሚኒስቴር ሚኒስትር ዶ/ር ሊያ ታደሠ እንደተናገሩት የጤና መድህን አባላትን ቁጥር በማሳደግ የዜጎችን ተጠቃሚነት የማረጋገጡ ስራ በ2014 በጀት ዓመትም ተጠናክሮ ሊቀጥል እንደሚገባ አሳስበዋል፡፡


የጤና መድህን አባላትን ቁጥር በማሳደግና ዘላቂነት ያለው የፋይናንስ ስርዓትን በመፍጠር በጤና ተቋማት ላይ የሚነሱ ችግሮችን ለመቅረፍ እንደሚረዳ የገለጹት ሚኒስትር ዶ/ር ሊያ ታደሠ ይህንን ለማሳካትም ከላይ እስከታች ያለው የጤና መዋቅር አመራር በመደጋገፍና በቅንጅት መንፈስ ሊሰራ ይገባልም ብለዋል፡፡

ፖሊዮን ጨርሶ ለማጥፋት የሚያስችል የክትባት ዘመቻ  በይፋ ተጀመረ

Dr. Dereje Duguma

ከፖሊዮ ነጻ የሆነ አለም እንፍጠር በሚል መሪ ቃል በአገር አቀፍ ደረጃ በሲዳማ ክልል በአዋሳ ከተማ እና በደቡብ ክልል ጌዲዮ ዞን ዲላ ከተማ የክትባት ዘመቻ መርሀግብር ያስጀመሩት የጤና ሚኒስትር ዴኤታ ዶ/ር ደረጀ ዱጉማ  በመርሀግብሩ እንደተናገሩት የጤና ሚኒስቴር ፖሊዮን ለማጥፋት በመደበኛ ክትባትና በዘመቻ በሚሰጥ ክትባት ከሀገራችን  ለማጥፋት ከፍተኛ ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ ነው።


ባለፉት አመታትም በተከናወነው ስራ ፖሊዮን ማጥፋት ተችሎ የነበረ ሲሆን በአሁኑ ወቅት  በተለያዩ አከባቢዎች  እየታየ ያለውን የልጅነት ልምሻ በሽታ ለማጥፋትም እስከ ጤና ኬላ በተዘረጋ መዋቅር እና ከአጋር አካላት ጋር በተቀናጀ አሰራር እየተተገበረ መሆኑን ተናግረው  ይህም መንግስት ለሕጻናት ጤና መሻሻል ትልቅ ትኩረት ሰጥቶ እንደሚሰራ ማሳያ መሆኑን አስረድተዋል፡፡ 

በጤናው ዘርፍ የክረምት በጎ ፍቃድ አገልግሎት የሰጡ የአዲስ አበባ ወጣቶች እውቅና ተሰጣቸው

youth

የጤና ሚኒስቴር ከአዲስ አበባ ወጣቶች በጎ ፍቃድ ማስተባበሪያ ቢሮ ጋር በመተባበር በጤናው ዘርፍ የክረምት የበጎ ፍቃድ አገልግሎት የእውቅና አሰጣጥ መርሃ ግብር በዛሬው እለት አካሂዷል፡፡ 


እውቅናውን  የተሰጣቸው የአዲስ አበባ ወጣቶች ሲሆኑ በቅዱስ አማኑኤል የአዕምሮ ስፔሻላይዝድ  ሆስፒታል፣ በአለርት ማእከል፣ በቅዱስ ጴጥሮስ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል፣ በጥሩነሽ ቤልጂንግ  ሆስፒታል፣ በካቲት 12 ሜዲካል ኮሌጅ፣ በራስ ደስታ ሆስፒታል እና በቅዱስ ጳውሎስ ሆስፒታል ሚሊኒዬም ሜዲካል ኮሌጅ ወስጥ የበጎ ፈቃድ አገልግሎት ሲሰጡ የቆዩ ወጣቶች ናቸው፡፡


የእውቅና አሰጣጥ መድረኩን በንግግር የከፈቱት የጤና ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴኤታ ዶክተር አየለ ተሾመ እንደ ጤና ሴክትር ብዙ ነገሮችን በገንዘብ እጥረት ምክንያት ማሳካት በማንችልበት አገር ውስጥ የበጎ ፈቃደኝነት አገልግሎት  መሰረታዊ ጉዳይ እንደሆነ ገልፀዋል፡፡

በአሜሪካ መንግስት 453,600 ዶዝ ጆንሰን ጆንሰን ኮቪድ19 ክትባቶች ለኢትዮጵያ ድጋፍ ተደረገ 

donation


ከአሜሪካ መንግስት ዓለም አቀፍ የኮቪድ-19 ወረርሽኝ ስርጭትን ለመከላከል 453,600 ዶዝ ጆንሰን ጆንሰን ኮቪድ19 ክትባቶች ለኢትዮጵያ ድጋፍ ተደረገ ፡፡


በርክክቡ ስነ ስርዓት ላይ የተገኙት የጤና ሚኒስትር ዴኤታ ወ/ሮ ሰሐረላ አብዱላሒ ባደረጉት ንግግር ከአሜሪካ መንግስት ወደ ኢትዮጵያ የገባው ክትባት ለአራተኛ ዙር እንደሆነ እና በዛሬው እለትም 453,600 ዶዝ ጆንሰን ጆንሰን ኮቪድ19 ክትባቶችን መረከባቸውን እንዲሁም በቀጣይ ተጨማሪ 504 ሺ ክትባቶች እንደሚገቡ ይፋ አድርገውዋል፡፡

የጤና ሚኒስቴር ከፍተኛ የስራ ሀላፊዎች በደቡብ ወሎ ኮምቦልቻ ከተማ በመገኘት ከቤት ንብረታቸው ተፈናቅለው በጊዜያዊ መጠለያ የሚገኙ ዜጎች የሚያገኙትን የጤና አገልግሎት በተመለከተ ምልከታ አካሄዱ 

Dr Dereje

በጥፋት ሀይሎች ለተጎዱ የጤና ተቋማትና በችግሩ የተፈናቀሉ ዜጎችን ጤንነት ለመጠበቅ  የሚደረጉ ድጋፎች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ ተገልጻል።
የጤና ሚኒስትር ዴኤታ ዶ/ር ደረጀ ዱጉማ እና የሚኒስቴሩ የእናቶች እና ህጻናት ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር  ዶ/ር መሰረት ዘላለም ከኮንቦልቻ ከተማ ከንቲባ እና ከጤና መምሪያ የስራ ሃላፊዎች ጋር በመሆን በመጠለያ የሚገኙ ዜጎችን ጎብኝተዋል።


በጉብኝቱ ወቅትም ከዩኤንኤፍፒኤ (UNFPA) በድጋፍ የተገኙ 590ሺ ዶላር ግምት ያላቸው የተለያዩ የንጽህና መጠበቂያ ቁሳቁሶችን፣ የስነ ተዋልዶ ኪቶችን፣ የኮቪድ መከላከያ ግብዓቶች የተረከቡ ሲሆን በርክክቡ ወቅትም ዶ/ር ደረጀ  ዱጉማ እንደተናገሩት  የጥፋት ሀይሎች በጤና ተቋማት ያደረሱትን ውድመት እና ዝርፍያ እንደዚሁም የበርካታ ዜጎችን ከቤት ንብረታቸው መፈናቀላቸውን በዚህም ለተለያዩ የጤና ጉዳቶች መጋለጠቸውን ጠቅስው በዩኤንኤፍፒኤ (UNFPA) በኩል የተደረገው ድጋፍ በአስፈላጊ  ወቅት እና አካባቢ መደረጉንም ገልጸዋል። 

"ወደ ሀገር ዉስጥ የሚገቡ ክትባቶችን በቁጥርም በአይነትም በመጨመር የአገልግሎቱ ተደራሽነት እየሰፋ ነዉ" ዶ/ር ሊያ ታደሰ

Dr lia tadesse

የጤና ሚኒስትር ዶ/ር ሊያ ታደሰ የኮቪድ-19 ወረርሽኝ በሀገራችን ያለበትን ሁኔታና በኮቪድ-19 ክትባት ዙሪያ መግለጫ ሰጥተዋል፡፡
ከጥቂት ሳምንታት በፊት በሀገራችን የወረሽኙ ምጣኔ በአንፃራዊ ሁኔታ ከነበረበት የመቀነስ አዝማሚያ አሳይቶ እንደነበር ያስታወሱት ሚኒስትሯ ካለፉት 3 ሳምንታት ጀምሮ ግን በሳምንታዊ ሪፖርት በበሽታው የመያዝ መጠን በ 4 እጥፍ ጭማሪ፣ በጽኑ የሚታመሙ ሰዎች በ2.5 እጥፍ ጭማሪ፣ ህይወታቸውን የሚያጡ ወገኖች ደግሞ በ2.8 እጥፍ ጭማሪ ማሳየቱንና ይህም አሳሳቢ እንደሆነ ገልፀዋል።  


ነገር ግን በሀገራችን ወረርሽኙን ለመከላከል የሚወሰዱ እርምጃዎች ትግበራ እየቀነሰ በመምጣቱ በሌሎች በርካታ የአፍሪካ ሀገራት እየተከሰተ ያለው ሦስተኛ ዙር የኮቪድ-19 በሽታ የስርጭት ማእበል ችግር በኢትዮጵያ እንዳይመጣ ህብረተሰቡ ጥንቃቄ እንዲያደርግ አሳስበዋል፡፡

echis

eCHIS

የኤሌክትሮኒክ የማህበረሰብ አቀፍ ጤና የመረጃ ስርዓት (eCHIS) በመረጃ አብዮት ከፍተኛ ትኩረት ከተሰጣቸው ዋና
ተግባራት መካከል አንዱ ነው። የኢትዮጲያ የጤና አክስቴንሽን ፕሮግራም ስኬታማ ሆኖ በማህበረሰብ ደረጃ ለውጥ ማምጣት
የቻለ እሳቤ ሲሆን፣ የዚህ እሳቤ አንዱ አካል በወረቀት ላይ የተመሰረትው የመረጃ ስርዓቱ ነው። eCHIS ይህን ከ1997
ዓ.ም ጀምሮ ሲሰራበት የነበረውን የወረቀት የመረጃ ስርዓት (CHIS) ወደ ኤሌክትሮኒክ ለመቀየር ታልሞ የተፈጠረ ነው።
በዚህም ዘመናዊ የመረጃ ስርዓትን ለጤና አክስቴንሽን ሰራተኞች በማቅረብ የሚከተሉትን ለማሳካት ተችሏል:-

የሳንባ ነቀርሳ እና የሥጋ ደዌ በሽታ(TBL)

leprosy

ሚና እና ኃላፊነት

  • በታካሚው መንገድ ላይ ያሉ ክፍተቶችን ማስተካከል
  • ኢንፌክሽን እና አክቲቭ በሽታን መከላከል።
  • ሰዎችን ማዕከል ያደረገ፣ ፍትሃዊ፣ ጥራት ያለው የTBL አገልግሎቶችን ማቅረብ።
  • ደፋር ፖሊሲዎችን ማጎልበት እና የድጋፍ ስርዓቶችን ማጠናከር።
  • የTBL ስትራቴጂካዊ መረጃን እና የምርምር ውጤቶችን ማምረትና መጠቀም

 

የፕሮግራም ምዕራፍ ፣ ፕሮጀክት እና ተነሳሽነት

 

ተላላፊ ያልሆኑ በሽታዎች(NCDs) መከላከል እና መቆጣጠር

non communicable diseases

የNCD መርሃ ግብር አጠቃላይ ግብ ጤናማ የአኗኗር ዘይቤዎችን በማስተዋወቅ፣ የተለመዱ የበሽታ መንስኤዎችን በመቀነስ እና የተቀናጀ ማስረጃን መሠረት ያደረገ፣ የፈጠራ እና ወጪ ቆጣቢ የህዝብ ጤና እና ክሊኒካዊ ጣልቃ ገብነትን በማቅረብ ተላላፊ ያልሆኑ በሽታዎችን ሸክም መቀነስ ነው።

የካርዲዮቫስኩላር በሽታዎች (CVD)፣ ሥር የሰደደ የመተንፈሻ አካላት በሽታዎች (CRD) ፣ ካንሰር ፣ የዓይን ጤና እና የስኳር በሽታ (DM) በሚኒስቴሩ ውስጥ እየተሰራባቸው ያሉ አራት ዋና የNCD ተነሳሽነቶች ናቸው።