Articles

"ማህበራዊ የባህሪ ለውጥ ለዘላቂ ልማት" በሚል መሪ ቃል 3ኛው ሀገር አቀፍ የማህበራዊና የባህሪ ለውጥ ጉባኤ በአዲስ አበባ በመካሄድ ላይ ይገኛል፡፡

Dr. Mekdes Daba

ጤና ሚኒሰቴር ከኢትዮጵያ ጤና ትምህርትና ፕሮሞሽን ባለሙያዎች ማህበር እንዲሁም ከአጋር አካላት ጋር በመተባበር ሶስተኛውን ሃገር አቀፍ የማህበራዊ እና ባህሪ ለውጥ ጉባዔ “የማህበራዊ እና ባህሪ ለውጥ ተግባራት ለዘላቂ የጤና ልማት” በሚል መሪ ቃል ከ13 አለም አቀፍ አገራት ከመጡ የዘርፉ ባለሙያዎችን ጨምሮ 400 በላይ ተሳታፊዎች በተገኙበት በአዲስ አባባ በማካሄድ ላይ ይገኛል፡፡

ዩኤስኤአይዲ( USAID) 156 የጅን ኤክስፕርት ማሽኖች ድጋፍ ለጤና ሚኒስቴር አድርጓል

USAID

ድጋፉ ሶስት ሚሊዮን የአሜሪካን ዶላር ወጪ የተደረገበት ሲሆን የቲቢ ፈጣን ሞለኪውላር ምርመራ በማድረግ የቲቢ በሽታን በፍጥነት ለማግኘት የሚያስችል ቴን ከለርድ የጂን ኤክስፐርት ማሽኖች ድጋፍ መሆኑ ታውቋል፡፡ በድጋፍ የተገኙት የጂን ኤክስፐርት ማሽኖቹ በተለይ ለተጎጂ ክልሎች እና የቲቢ ስርጭት ላለባቸው አካባቢዎች ላይ ላሉ ጤና ተቋማት እንደሚተላለፉ ተገልጿል።

የጤና ሚኒስትር ዴኤታ ዶክተር ደረጀ ድጉማ በድጋፉ የርክክብ ስነስርዓት ላይ እንደተናገሩት የጤና ሚኒስቴር የሳንባ ነቀርሳን ለማጥፋት አዲስ የ7 ዓመታት ስትራቴጂክ እቅድ ማዘጋጀቱንና ዩኤስኤአይዲ ኢትዮጵያ በአዲሱ ስትራቴጂክ ዕቅድ ውስጥ ቁልፍ ሚና እንደነበረው ጠቅሰው ለእቅዱ ስኬት መረጃን መሰረት ባደረገ፤ ውጤታማ በሆነ መንገድ መተግበርን ይጠይቃል ብሏል።

በኢትዮጵያ በአዲስ ቴክኖሎጂ ህክምና የሚሰጥ የመጀመሪያው የስትሮክ ህክምና ማእከል በዛሬው እለት ተመርቆ ተከፍቷል።

stroke treatment center

የጤና ሚኒስትር ዶክተር ሊያ ታደሠ በምርቃት ስነስርዓቱ ላይ ተገኝተው ባደረጉት ንግግር እንዳሉት የጤናው ዘርፍ በርካታ መሻሻሎች እያሣየ ያለ ቢሆንም ገና ብዙ ወደ ፊት መሄድ ይጠበቅበታል ብለዋል። የአክሶል ስትሮክ እና ስፓይን ማእከል መከፈቱ እንደ ሀገር የእስትሮክ ህክምናን አንድ ምእራፍ ወደ ፊት የሚወስድ መሆኑን ጠቅሰው ማእከሉ  ለዚህ ምረቃ በመድረሱ ያላቸውን አድንናቆት ገልጸዋል። ይህ አዲስ ቴክኖሎጂ እና የተለየ አገልግሎት ይዞ የመጣ ማእከል በአገሪቱ መከፈት መቻሉ ለጤናው ዘርፍ ትልቅ አስተዋጽኦ እንደሚኖረውም ዶክተር ሊያ ተናግረዋል።


ላለፋት አመታት ተላላፊ ያልሆኑ በሽታዎች እና በዚህ ሳቢያ የሚመጣ ሞት እየጨመረ መምጣቱን የገለጹት ዶክተር ሊያ ይህን ችግር ለመቅረፍ የጤና ሚኒስቴር ከመከላከል ስራው ጎን ለጎን የስፔሻሊቲ ህክምና አገልገግሎት ማስፋፋት ስራ የሚያሰራ የአስር አመት ፍኖተ ካርታ  ተዘጋጅቶ እየተተገበረ መሆኑን አስረድተዋል።