Articles

አባቶች፣ የቤተሰብ አባላትና ማህበረሰቡ ለሚያጠቡ እናቶች ትኩረት ሊሰጡ ይገባል

group picture

"ምቹ ሁኔታ ለሚያጠቡ እናቶች፣ እናስተምር፣ እንደግፍ!!" በሚል መሪ ቃል በአለም ለ30ኛ ጊዜ በሃገራችን ደግሞ ለ14ኛ ጊዜ የጡት ማጥባት ሳምንት እየተከበረ ሲሆን ዛሬ በደብረብርሃን ወይንሸት የተፈናቃዮች መጠለያ ከሚገኙ እናቶችና ህጻናት ጋር በአሉ ተከብሯል። 


በጤና ሚኒስቴር ሃገር አቀፍ የስርዓተ ምግብ ፕሮግራም አስተባባሪ የሆኑት ወ/ሮ ህይወት ዳርሰኔ በስነስርዓቱ ላይ እንደ ተናገሩት እናቶች ልጆቻቸውን እስከ ስድስት ወራት ጡት ብቻ ማጥባታቸው የህጻኑን ጤንነት ከመጠበቅና የተስተካከለ እድገት እንዲኖረው ከማስቻሉ ባለፈ ሃገራዊ ጥቅሙ ከፍተኛ ነው ብለዋል። እናቶች በማይመች ሁኔታ ውስጥም ቢሆኑ ለልጆቻቸው የጡት ወተትን መስጠት ማቋረጥ እንደሌለባቸው ለእናቶቹ አስገንዝበው አባቶች፣ የቤተሰብ አባላትና ማህበረሰቡም ለሚያጠቡ እናቶች ትኩረት ሊሰጡ እንደሚገባ አስገንዝበዋል።

የኮሪያ መንግስት በኮፍ /KoFIH / ግብረሰናይ ድርጅት እና ኤክዚም ባንክ በኩል ለጤና ሚኒስቴር የኮቪድ 19 የዲያግኖስቲክ ላብራቶሪ ቁሳቁሶችን ድጋፍ አደረገ

The Korean government

በርክክብ ሥነ ሥርዓቱ ላይ የተገኙ የጤና ሚኒስቴር  ሚኒስትር ዶ/ር ሊያ ታደሰ የኮሪያ መንግሥት በተለያዩ ሥራዎች የጤና ሴክተሩን እንደሚያግዝ ተናግረው ይበልጥ በእናቶችና ህፃናት ጤና፣ በጤና መድህን አገልግሎት፣ የህክምና ባለሙያዎች ስልጠና፣ የህክምና ቁሳቁስ ጥገና እና ኮቪድ-19ን መከላከልና መቆጣጠር እንዲሁም የፅኑ ህሙማን ህክምና መሣሪያዎች ላይ ያደረጉትን ድጋፍ  አንስተዋል፡፡ 


የተደረገው ድጋፍ የኮቪድ-19ን ለመከላከልና ለመቆጣጠር  ጠቀሜታ  የጎላ  እንደሆነ ዶ/ር ሊያ ታደሰ  የተናገሩ ሲሆን ይህ ድጋፍ የሁለቱ ሃገራት ጥብቅ ግንኙነት ያሳያል ብለዋል፡፡


የኮፍ /KoFIH / ግብረ ሰናይ ድርጅት ፕሬዘዳንት ኘ/ር ቺያግ ዩፐ ኪም የኢትዮጵያ እና የደቡብ ኮሪያ ግንኙነት ረጅም አመታት ያስመዘገበ መሆኑን አውስተው የኮቪድ-19 የዲያግኖስቲክ ላብራቶሪ ቁሳቁሶችን ድጋፍ በተጨማሪ የመጀመሪያ ደረጃ ጤና ሥርዓት ማጠናከር ላይ በትኩረት  እንደሚሠሩ ተናግረዋል፡፡

በክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎት በጋምቤላ ክልል የአቅመ ደካሞችን ቤት የማደስ ስራ ተጀመረ 

Dr. Lia Tadesse

በ2014 በጀት ዓመት በጤና ሚኒስቴር አስተባ ባሪነት ተጠሪ ተቋማትን ባከተተ መንገድ የተለያዩ የክረምት በጎፍቃድ ስራዎች እየተከናወኑ ይገኛል።


 የጤና ሚኒስትር ዶ/ር ሊያ ታደሰ በክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎት የአቅመ ደካሞችን ቤት የማደስ ማስጀመሪያ መርኃ ግብር ዛሬ በጋምቤላ ከተማ፣ የአቅመ ደካማ ቤቶች እድሳትን አስጀመሩ። በዚህም የ 5 አቅመ ደካሞች ቤት ሙሉ በሙሉ የሚታደስ ይሆናል።


በክልሉ የአቅመ ደካማ ወገኖችንን ቤት ከማደስ ፕሮግራም ማስጀመር በተጨማሪ  የጋምቤላ ከተማ የመጀመሪያ ደረጃ  ሆስፒታል  የድንገተኛ ህክምና አገልግሎት አሰጣጥ፣ በክልሉ የሚገነባው ሪጅናል ላብራቶሪ ግንባታ ሒደት፣ እንዲሁም አሻራችን ለትውልዳችን በሚል መሪ መልክት  በጋምቤላ ከተማ ጤና ጣቢያ የችግኝ ተከላ ተካሒዷል። 


 በመርሀ ግብሩም በክልሉ በዝቅተኛ ገቢ ከሚተዳደሩ የአቅመ ደካማ ልጆች ለ400 ተማሪዎች የትምህርት ቁሳቁስና ድጋፍ ተደርጓል።