Articles

የሚሊኒየም ኮቪድ ህክምና እና ድንገተኛ ምላሽ ማዕከል የምስጋና እና የማስረከብ ፕሮግራም ተከናወነ

የሚሊኒየም ኮቪድ ህክምና እና ድንገተኛ ምላሽ ማዕከል

የጤና ሚኒስቴር ላለፉት ሁለት ዓመታት የኮቪድ የህክምና እና የድንገተኛ ምላሽ ማዕከል ሆኖ ሲያገለግል የቆየውን አዲስ ፓርክ /የሚሊኒየም አዳራሽ/ ከምስጋና ጋር ለሜድሮክ ኢንቨስትመንት ግሩፕ አስረከበ።


የጤና ሚኒሰቴር ሚኒስትር ዶ/ር ሊያ ታደሰ ማዕከሉን ለሜድሮክ ኢንቨስትመንት ግሩፕ ባስረከቡበት ወቅት እንደገለፁት ባለፉት ሁለት ዓመታት የኮቪድ ወረርሽኝን ለመከላከል ብዙ ውጣ ውረዶች ማለፋቸውን ጠቅሰው ዛሬም ኮቪድ እያስከተለ ያለው ችግር ባይቆምም ለዚህ ዕለት በመብቃታችንና የሚሊኒየም የህክምና ማዕከልን መልሰን ማስረከብ በመቻላችን ደስተኞች ነን ብለዋል።

የቤተሠብ እቅድ አገልግሎትን ለማስፋፋት የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት የድርሻቸውን ሀላፊነት እንደሚወጡ ገለፁ። 

House of Representatives

ይህ የተገለፀው የጤና ሚኒስቴር በቤተሠብ እቅድ አገልግሎት ተደራሽነት፣ ስኬት እና ክፍተት በተመለከተ ለህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት ባደረገው የግንዛቤ መስጨበጫ መድረክ ላይ ነው። በመድረኩ ተገኝተው ንግግር ያደረጉት የጤና ሚኒስትር ዴኤታ ዶክተር ደረጀ ድጉማ እንዳሉት የቤተሠብ እቅድ አገልግሎት መስጠት የሴቶች እና ህጻናት ህይወት ለመታደግ ዋነኛው አቅጣጫ መሆኑን ጥናቶች እንደሚያመለክቱ ጠቅሰው ይህን አገልግሎት ተደራሽ ማድረግ ላይ ትኩረት ተሠጥቶ ሊሠራ እንደሚገባ ገልጸዋል።


ባለፉት አመታት በቤተሠብ እቅድ አገልግሎት የተሠሩ ሥራዎች እና የተገኙ መሻሻሎች እንደተጠበቁ ሆነው አሁንም 22 በመቶ የሚሆኑ በለትዳር ሴቶች አገልግሎቱን ለማግኘት ቢፈልጉም ተደራሽ ማድረግ አለመቻሉን የገለጹት ሚኒስትር ድኤታው ይህም በበጀት አመቱ የገንዘብ እጥረት በማጋጠሙ ምክንያት መሆኑም አስረድተዋል።

የቦሩ ሜዳ ጠቅላላ ሆስፒታል በጦርነት ከደረሰበት ጉዳት አገግሞ ሁሉንም አገልግሎቶች በመስጠት ላይ ነው::

Boru Meda General Hospital

የጤና ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴኤታ ዶ/ር አየለ ተሾመ የሆስፒታሉን የተለያዩ የስራ ክፍሎች ተዘዋውረው በጎበኙበት ወቅት እንደገለፁት ሆስፒታሉ ከደረሱበት ችግሮች ፈጥኖ በማገገም ለተገልጋዮች የተሟላ አገልግሎት መስጠት መጀመሩ የሚደነቅ ነው ብለዋል።


የቦሩ ሜዳ ጠቅላላ ሆስፒታል በጦርነቱ ወቅት ከፍተኛ ውድመት ከደረሰባቸው ሆስፒታሎች አንዱ እንደነበር ያስታወሱት ዶ/ር አየለ የተሟላ አገልግሎት እንዲሰጥ የተረባረቡትን ሁሉ አመስግነው በቀጣይም የጤና ሚኒስቴር የጎደሉ የህክምና መሳሪያዎችን ለማሟላት እየተፈፀሙ ያሉ ግዢዎችን በማፋጠን ሆስፒታሉ የሚጠናከርባቸውን አማራጮች ሁሉ እንደሚያመቻች ተናግረዋል።