Articles

የኮሪያ አለም አቀፍ ትብብር ኤጀንሲ (ኮይካ) ለጤና ሚኒስቴር የእናቶችና ጨቅላ ህጻናት ጤናን ለማሻሻል የሚረዳ የህክምና ቁሳቁሶችን ድጋፍ አደረገ::

Dr. Lia Tadesse

የኮሪያ አለም አቀፍ ትብብር ኤጀንሲ (ኮይካ) ለጤና ሚኒስቴር 31,076,584 ብር የሚያወጣ የህክምና ቁሳቁስ ድጋፍ ,በቤንሻንጉል ጉሙዝ እና አፋር ክልሎች የእናቶችና የጨቅላ ህጻናት ጤናን ለማሻሻል በዩኒሴፍ አመቻችነት የኮሪያ አለም አቀፍ ትብብር ኤጀንሲ (ኮይካ) ባደረገው  የገንዘብ ድጋፍ የህክምና መሳሪያዎች እና ለትራንስፖረት አገልግሎት የሚውሉ ሞተር ሳይክሎችን ለጤና ሚኒስትር አስረክቧል፡፡

የጤና ሚኒስቴር ከቻይና መንግስት 10 ሚሊዮን ዶዝ የኮቪድ 19 ክትባት ተረከበ።

from the Chinese

የቻይና መንግስት ከዚህ ቀደም ለኢትዮጵያ ቃል ገብቶት ከነበረው የ20 ሚሊዮን ዶዝ የኮቪድ 19 ክትባት ውስጥ 10 ሚሊዮኑን የጤና ሚኒስትር ዶ/ር ሊያ ታደሰ የቻይና የኢትዮጵያ አምባሳደር ከሆኑት ዛኦ ዚያን እጅ በዛሬው እለት  ተረክበዋል፡፡ 


በርክክቡ ወቅት የጤና ሚኒስቴር ሚኒስትር ዶ/ር ሊያ ታደሰ የቻይና መንግስት የኮቪድ 19 በሽታን ለመከላከል የሚደረገውን ጥረት ለማገዝ እያደረገው ስላለው እገዛ ምስጋና አቅርበዋል። ለኢትዮጵያ ድጋፍ ከተደረገው 10 ሚሊዮን ውስጥ 5 ሚሊየን የሚሆነው በቻይና መንግስት ቀዳማዊት እመቤት የተበረከተ ሲሆን በአቻቸው የኢትዮጵያ ቀዳማዊት እመቤት ወ/ሮ ዝናሽ ታያቸው ስም ለጤና ሚኒስቴር የደረሰ መሆኑን የጠቀሱት ዶ/ር ሊያ ክትባቱም በዋነኝነት ተደራሽ የሚያደርገው ለእናቶች እና ለወጣቶች መሆኑንም አክለው ተናግረዋል፡፡ 

በመጀመሪያ ደረጃ ጤና ክብካቤ ፕሮጀክት ባለፉት ስድስት አመታት ከ58 ሚሊዮን በላይ የህብረተሰብ ክፍሎች ጥራት ያለው የጤና አገልግሎት አግኝተዋል።

Dr. Lia Tadesse

የመጀመሪያ ደረጃ ጤና እንክብካቤ ፕሮጀክት በማስተባበር ፓዝፋይንደር ከአሜሪካ እና ከኮሪያ ህዝብና መንግስት በሚደረግለት ድጋፍ ባለፉት ስድስት አመታት በስድስት ክልሎችና በ451 ወረዳዎች ፕሮጀክቶችን ሲሰራ መቆየቱን ዶ/ር ሊያ ታደሰ የጤና ሚኒስቴር ሚኒስትር ተናግረዋል፡፡

የጤና ሚኒስቴር ከዩኤስኤአይዲ ትራንስፎርም  ፕኤችሲዩ ጋር በመተባበር በመጀመሪያ ደረጃ ጤና እንክብካቤ በኦሮሚያ፣ በአማራ፣ በደቡብ፣ በሲዳማ፣ በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ እና በትግራይ ክልል ጤና ቢሮዎችና አጋር ድርጅቶች ጋር በመተባበር ጥራት ያለው የስነ ተዋልዶ፣ የእናቶች፣ የጨቅላ ህፃናት፣ ታዳጊዎችና ወጣቶች እንዲሁም የስነ ምግብ አገልግሎቶች ተግባራዊ መደረጋቸው ዶ/ር ሊያ ታደሰ አንስተዋል፡፡