Articles

በጤና ሚኒስትር ክብርት ዶ/ር ሊያ ታደሰ የሚመራ የኢትዮጵያ ልዑካን ቡድን በ75 ኛው የአለም ጤና ጉባኤ ላይ እየተሳተፈ ነው።

World Health Assembly

የኮቪድ 19 ወረርሽኝ ከተከሰተ ወዲህ በአካል የመጀመሪያ የሆነው ይህ የጤና ጉባኤ ግንቦት 14, 2014 ዓ.ም  በጄኔቫ ዝዊዘርላንድ በይፋ ተጀምሯል። 


"ሰላም ለጤና ጤና ለሰላም!"( "Peace for Health and Health for peace!") በሚል መሪ ቃል እየተካሄደ ያለው 75 ኛው የአለም ጤና ጉባኤ ላይ የአለማችን የማህበረሰብ ጤና  አሁናዊና ቀጣይ  ስትራቴጅክ ጉዳዮች ቀርበው ምክክርና ውይይት የሚደረግ ሲሆን ጉባኤው ለአንድ ሳምንት በጄኔቫ የሚቀጥል ይሆናል።

በኢንዶኔዢያ ጃካርታ በውሃ፣ በሳኒቴሽን እና በሃይጅን ርዕሰ ጉዳዮች ላይ ከ37 ሀገራት የተውጣጡ የዘርፉ ሚኒስትሮች የልምድ ልውውጥ እና ውይይት እያካሄዱ ነው

 በውሃ፣ በሳኒቴሽን እና በሃይጅን ርዕሰ ጉዳዮች ላይ ከ37 ሀገራት የተውጣጡ የዘርፉ ሚኒስትሮች የልምድ ልውውጥ እና ውይይት

በመድረኩ በዓለም መንግስታት የሚደገፍ መንግስታዊ እና መንግስታዊ ያልሆኑ ሲቪክ ማህበራት፣ የተባበሩት መንግስታት ኤጀንሲዎች፣ የልማት ባንኮች እና ሌሎች ባለድርሻ አካላት የተገኙ ሲሆን ውይይቱ በዘላቂ የልማት ግብ 6 ማለትም ዘላቂ የመሰረታዊ ውሃ፣ ሳኒቴሽን እና ሀይጅን አገሌግሎት ለሁሉም ማዳረስ ላይ ያጠነጠነ ነው።

በጃካርታ እየተካሄደ ያለው መድረክ በዋነኝነት በ2030 እ.ኤ.አ የውሃ፣ ሳኒቴሽን እና ሀይጅን አገልግሎቶችን ግብ ለማሳካት ወሳኝ በሆኑት የፖለቲካ ቁርጠኝነት፣ተጨማሪ ኢንቨስትመንት፣ አመራር እና ተጠያቂነት ላይ ትኩረት ያደረገ ነው ተብሏል።

በሁለት ቀናት ቆይታው ከውሃ፣ ከሳኒቴሽን እና ከሃይጅን ርዕሰ ጉዳዮች በተጨማሪ የጎንዮሽ ውይይቶች በዘርፉ ሚኒስትሮች ይደረጋሉ ተብሎ ይጠበቃል፡፡

በሀገራችን ያለውን መሰረታዊ የጤና አገልግሎት ፋይናንስ ስርዓት ለማጠናከር የሚያችል አውደ ጥናት ተካሄደ 

basic health care financial system

በቅርቡ የታተመው የላንሴት ግሎባል የጤና ኮሚሽን ሪፖርት ላይ በማተኮር "የህብረተሰብ ጤና ክብካቤ ላይ መዋዕለ ንዋይ በማፍሰስ ሰውን ማስቀደም" በሚል መሪ ቃል የጤና ሚኒስቴር ሚኒስትር ዶክተር ሊያ ታደሰ በተገኙበት የመጀመሪያ ደረጃ የጤና ክብካቤ ፋይናንስ ላይ ትኩረቱን ያደረገ መድረክ የክልል ጤና ቢሮ ኃላፊዎች የጤና ሚኒስቴር ተጠሪ ተቋማት እንዲሁም የገንዘብ ሚኒስቴር እና አጋር ድርጅቶችን በማካተት አውደ ጥናት አካሄዷል፡፡


በአገራችን በሽታን በመካከልና ጤና ማበልጸግ ፖሊሲን በመቅረጽ የመጀመሪያ ደረጃ የጤና አጠባበቅ ዘዴን ተግባራዊ እየተደረገ እንደሚገኝና የጤና ኤክስቴንሽን መርሃ ግብር ማሻሻያ ፍኖተ ካርታንም በመዘርጋት ሞዴል ወረዳዎችን ለመፍጠር፣ የማህበረሰብ አቀፍ የጤና መድህን ሸፋንን ለማሳደግ እና ሁሉንም የጤና ተቋማት ወደ ከፍተኛ አፈጻጸም ለመቀየር በመላ ሀገሪቱ እየተሰራበት እንደሚገኝ ሚኒስትር ዶ/ር ሊያ ተደሰ በመድረኩ ላይ ተናግረዋል፡፡