Articles

በአሜሪካ መንግስት 453,600 ዶዝ ጆንሰን ጆንሰን ኮቪድ19 ክትባቶች ለኢትዮጵያ ድጋፍ ተደረገ 

donation


ከአሜሪካ መንግስት ዓለም አቀፍ የኮቪድ-19 ወረርሽኝ ስርጭትን ለመከላከል 453,600 ዶዝ ጆንሰን ጆንሰን ኮቪድ19 ክትባቶች ለኢትዮጵያ ድጋፍ ተደረገ ፡፡


በርክክቡ ስነ ስርዓት ላይ የተገኙት የጤና ሚኒስትር ዴኤታ ወ/ሮ ሰሐረላ አብዱላሒ ባደረጉት ንግግር ከአሜሪካ መንግስት ወደ ኢትዮጵያ የገባው ክትባት ለአራተኛ ዙር እንደሆነ እና በዛሬው እለትም 453,600 ዶዝ ጆንሰን ጆንሰን ኮቪድ19 ክትባቶችን መረከባቸውን እንዲሁም በቀጣይ ተጨማሪ 504 ሺ ክትባቶች እንደሚገቡ ይፋ አድርገውዋል፡፡

የጤና ሚኒስቴር ከፍተኛ የስራ ሀላፊዎች በደቡብ ወሎ ኮምቦልቻ ከተማ በመገኘት ከቤት ንብረታቸው ተፈናቅለው በጊዜያዊ መጠለያ የሚገኙ ዜጎች የሚያገኙትን የጤና አገልግሎት በተመለከተ ምልከታ አካሄዱ 

Dr Dereje

በጥፋት ሀይሎች ለተጎዱ የጤና ተቋማትና በችግሩ የተፈናቀሉ ዜጎችን ጤንነት ለመጠበቅ  የሚደረጉ ድጋፎች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ ተገልጻል።
የጤና ሚኒስትር ዴኤታ ዶ/ር ደረጀ ዱጉማ እና የሚኒስቴሩ የእናቶች እና ህጻናት ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር  ዶ/ር መሰረት ዘላለም ከኮንቦልቻ ከተማ ከንቲባ እና ከጤና መምሪያ የስራ ሃላፊዎች ጋር በመሆን በመጠለያ የሚገኙ ዜጎችን ጎብኝተዋል።


በጉብኝቱ ወቅትም ከዩኤንኤፍፒኤ (UNFPA) በድጋፍ የተገኙ 590ሺ ዶላር ግምት ያላቸው የተለያዩ የንጽህና መጠበቂያ ቁሳቁሶችን፣ የስነ ተዋልዶ ኪቶችን፣ የኮቪድ መከላከያ ግብዓቶች የተረከቡ ሲሆን በርክክቡ ወቅትም ዶ/ር ደረጀ  ዱጉማ እንደተናገሩት  የጥፋት ሀይሎች በጤና ተቋማት ያደረሱትን ውድመት እና ዝርፍያ እንደዚሁም የበርካታ ዜጎችን ከቤት ንብረታቸው መፈናቀላቸውን በዚህም ለተለያዩ የጤና ጉዳቶች መጋለጠቸውን ጠቅስው በዩኤንኤፍፒኤ (UNFPA) በኩል የተደረገው ድጋፍ በአስፈላጊ  ወቅት እና አካባቢ መደረጉንም ገልጸዋል። 

"ወደ ሀገር ዉስጥ የሚገቡ ክትባቶችን በቁጥርም በአይነትም በመጨመር የአገልግሎቱ ተደራሽነት እየሰፋ ነዉ" ዶ/ር ሊያ ታደሰ

Dr lia tadesse

የጤና ሚኒስትር ዶ/ር ሊያ ታደሰ የኮቪድ-19 ወረርሽኝ በሀገራችን ያለበትን ሁኔታና በኮቪድ-19 ክትባት ዙሪያ መግለጫ ሰጥተዋል፡፡
ከጥቂት ሳምንታት በፊት በሀገራችን የወረሽኙ ምጣኔ በአንፃራዊ ሁኔታ ከነበረበት የመቀነስ አዝማሚያ አሳይቶ እንደነበር ያስታወሱት ሚኒስትሯ ካለፉት 3 ሳምንታት ጀምሮ ግን በሳምንታዊ ሪፖርት በበሽታው የመያዝ መጠን በ 4 እጥፍ ጭማሪ፣ በጽኑ የሚታመሙ ሰዎች በ2.5 እጥፍ ጭማሪ፣ ህይወታቸውን የሚያጡ ወገኖች ደግሞ በ2.8 እጥፍ ጭማሪ ማሳየቱንና ይህም አሳሳቢ እንደሆነ ገልፀዋል።  


ነገር ግን በሀገራችን ወረርሽኙን ለመከላከል የሚወሰዱ እርምጃዎች ትግበራ እየቀነሰ በመምጣቱ በሌሎች በርካታ የአፍሪካ ሀገራት እየተከሰተ ያለው ሦስተኛ ዙር የኮቪድ-19 በሽታ የስርጭት ማእበል ችግር በኢትዮጵያ እንዳይመጣ ህብረተሰቡ ጥንቃቄ እንዲያደርግ አሳስበዋል፡፡