Articles

በጅግጅጋ ከተማ የተካሄደው 23ኛው የጤና ዘርፍ ጉባኤ የ2014 ዓ.ም ዕቅድን በጋራ ለማሳካት የሚያስችል የቃል ኪዳን ስምምነት ከክልሎችና ከተማ መስተዳድሮች ጋር በመፈራረም ተጠናቋል

final

"ምላሽ ሰጪ የጤና ስርዓት በአዲስ ምዕራፍ " በሚል መሪ ቃል ለሶስት ቀናት በጅግጅጋ ከተማ ሲከናወን የቆየው 23ኛው የጤናው ዘርፍ ዓመታዊ ጉባዔ ተጠናቋል።


በጉባኤው ማጠናቀቂያ ላይ የጤና ሚኒስትር ዶ/ር ሊያ ታደሰ ከዘጠኝ የክልልና ሁለት የከተማ መስተዳድር የጤና ቢሮ ኃላፊዎች ጋር ባደረጉት ስምምነት መሠረት በበጀት ዓመቱ የተቀመጡ ዕቅዶችን በጋራ ለማሳካት የሚያስችሉ ግብዓቶችን በማሟላትና የተቀናጀ ርብርብ በማድረግ ለህብረተሰቡ ተገቢውንና ጥራት ያለውን የጤና አገልግሎትፍትሃዊና ተገልጋይ ተኮር በሆነ መልኩ ለማቅረብ በስምምነት ፊርማቸው በጋራ ቃል ገብተዋል።


ጉባዔውን በንግግር የዘጉት የጤና ሚኒስቴር ሚኒስትር ዶ/ር ሊያ ታደሰ ጉባኤው በተሳካ ሁኔታ እንዲከናወን ያደረጉትን አጋር አከላት እና በተለይም የሶማሌ ክልልን ካመሰገኑ በኋላ ሁላችንም በያለንበት ለህብረተሰቡ ሁሉን አቀፍ የጤና አገልግሎት ለማዳረስ ተግተን መስራት ይገባናል ብለዋል።

ጠንካራ የፋይናንስና ፍትሃዊ የጤና ስርዓቶች ጥራት ላለው የጤና አገልግሎት

discussion

በጅግጅጋ በሚካሄደው የጤናው ዘርፍ ልማት ጉባኤ የሁለተኛ ቀን ውሎ ተሳታፊዎች በተለያዩ ጤና ጉዳዮች ላይ የፓናል ውይይት አካሂደዋል፡፡
የጤና ሚኒስትር ዶ/ር ሊያ ታደሠ እና የጤና ሚኒስትር ዴኤታ ወ/ሮ ሰሃረላ አብዱላሂ የተገኙበት የፓናል ውይይት የጤና ፋይናንስን እና ፍትሃዊነትን ማሻሻል ላይ ትኩረት ያደረገ ነበር፡፡


የጤና ፋይናንስ ስርዓቱን አስመልክቶ በቀረበው ፓናል ውይይት ከሃገር አቀፍና ከዓለም አቀፍ ድርጅቶች የሃብት ማሰባሰብ ስራዎች የተሰሩ ሲሆን መንግስት ከጠቅላላው በጀት ውስጥ 13 ነጥብ 2 በመቶ የሚሆነውን ለጤናው ዘርፍ እንዲመደብ ለማድረግ ተችሏል፡፡  
የግሉን የጤና ዘርፍና የመንግስትን ትብብር ለማጠናከር በተሰራው ስራ የግሉ ዘርፍ ተሳትፎ በተለይም የጤና ግብአቶች ምርትና ተርሸሪ ኬር ላይ እንዲጨምር ማድረግ መቻሉ በውይይቱ ተነስቷል፡፡ 

በጂግጂጋ ዩኒሸርሲቲ ሼህ ሀሰን የቦሬ ሪፈራል ሆሰፒታል የሚገኘው የኩላሊት እጥበት ማእከል እና የጂግጂጋ የደምና ቲሹ ባንክ በዛሬው እለት በጤና ሚኒስቴር ከፍተኛ አመራሮች ተጎብኝቷል

visit

የጤና ሚኒስቴር ከፍተኛ የስራ አመራሮች ከክልሉ የጤና ቢሮ የስራ ኃላፊዎች ጋር በመሆን በሆስፒታሉ የሚገኙ የMRI ክፍልን፣ የኩላሊት እጥበት ህክምና ማእከልን፣ የደምና ቲሹ ባንክን የጎበኙ ሲሆን በተለይ የከተማዋ ህብረተሰብና ባለሀብቶችን በማሳተፍ የተቋቋመው የኩላሊት እጥበት ህክምና ማእከል አገልግሎት አሰጣጥ ተዘዋዉረው ተመልክተዋል።


የኩላሊት እጥበት ህክምና ማእከሉ ከሱማሌ ና ከአካባቢው ለሚመጡ ተካሚዎች በተመጣጣኝ ዋጋ አገልግሎት ተደራሸ እያደረገ እንደሆነ በጉብኝቱ ተገልጿል። በዚህም በ2013 ዓ.ም ለ724 ታካሚዎች አገልግሎቱን መስጠት  እንደተቻለ ተገልጿል።


በተለይ የጂግጂጋ የደምና ቲሹ ባንክ የመረጃ ስርአቱን ዲጂታላይዝ የማድረግ ስራን ዶ/ር ሊያ ታደሰ በጉኝቱ ወቅት በይፋ ያሰጀመሩ ሲሆን የምርመራ ሂደቱን በአዉቶሜሸን በመታገዝ እየተከናወነ እንደሚገኝ ተመልክተዋል።