Articles

ከፍተኛ ውድመት የደረሰባቸውን የጤና ተቋማት ለማቋቋምና መልሶ ስራ ለማስጀመር እንዲቻል ከጤና ሚኒስቴር የቀረበ  ሁሉን-አቀፍ የድጋፍ ጥሪ!

Health Facility

አሸባሪው የጥፋት ቡድን ህወሓት በወረራ ይዟቸው በነበሩ አካባቢዎች ካደረሰው ሰብዓዊና ሞራላዊ ጥፋት በተጨማሪ  ህዝብ የሚገለገልባቸውን የጤና አገልግሎት ሰጪ ተቀቋማት፤ የህክምና ግብዓት ማከማቻ ተቋማትን እና ሌሎች ማህበራዊ ተቋማት አውድሟል፡፡ የህክምና መሳርያዎችን እና ሌሎች ግብዓቶችንም ጭኖ በመውሰዱ ዝርፍያ እና ጉዳት ፈጽሟል፡፡

 
በጤና ተቋማት ላይ የደረሰው ወድመት በተለይ ድጋፍ ለሚሹ ዜጎች የመሰረታዊ እና ድንገተኛ ህክምና አግልግሎት አሰጣጥ በእጅጉ አስተጓጉሏል። እስካሁን በደረስንበት መረጃ ከ2700 በላይ የሚሆኑ የጤና ተቋማት አገልግሎት የማይሰጡ ሲሆን በአሁን ወቅት በመንግስት ተደራሽ ያልሆኑ አከባቢዎች ሲካተቱ ዉድመት የደረሰባቸዉ ቁጥር ከዚህ እንደሚያሻቅብ ይጠበቃል።

በከፍተኛ ወጪ ተገንብተው አገልግሎት ሲሰጡ የነበሩ  የደሴና የኮምቦልቻ ጤና ተቋማት በአሸባሪውና ወራሪው የህውሃት ቡድን አገልግሎት እንዳይሰጡ ሆነው ወድመዋል፡፡      

health facility

በደሴ ከተማ የሚገኘው የደሴ አጠቃላይ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል በአሸባሪውና ወራሪው የህውሀት ቡድን አገልግሎት እንዳይሰጥ ሆኖ የወደመ ሲሆን ቡድን በተደራጀ መልኩ የህክምና መሳሪያዎችንና ሌሎች አስፈላጊ ግብዓቶችን ጭኖ ከመውሰዱ ባለፈ የቀሩትንም ጥቅም ላይ እንዳይውሉ አድርጎ ሙሉ በሙሉ አውድሟቸዋል።


ከእነዚህም መካከል በተኝቶ ህክምና፣ በፅኑ ህክምናና በአንስተኛና በከፍተኛ የቀዶ ህክምና ክፍሎች የነበሩ በብዙ ሚሊዮን ብር የተገዙ የትንፋሽ መስጫ /ventilator/ እና አንስቴዥያ ማሽኖች የተወሰዱ ሲሆን ቀሪዎቹ ደግሞ ሙሉ በሙሉ በመውደማቸው በአሁኑ ወቅት ሆስፒታሉ አገልግሎት መስጠት በማይችልበት ደረጃ ላይ ይገኛል።

የጤና ሚኒስቴር ለሀገር መከላከያ ሰራዊት 30 ሚሊዮን ብር እና 1.5 ሚልዮን ብር የሚገመቱ የተለያዩ የዓይነት ድጋፎችን አደረገ

donation

በድጋፍ ርክክቡ ላይ የጤና ሚኒስትር ዶ/ር ሊያ ታደሰ  እንደተናገሩት አሁን ላይ አገራችን እና ህዝቦቿ ከመቼውም በተለየ ከውስጥም ከውጪም ፈተናዎች  እና መሰናክሎች የገጠሟት ወቅት ላይ እንደምንገኝ ገልጸው በሁሉም መስኮች በማህበራዊ ፣ በፖለቲካዊ፣ በኢኮኖሚያዊ እና በውጭ ጉዳዮቻን ላይ የገጠሙን ችግሮች ለጊዜው ሊፈትኑን እና ሊከብዱን ቢችሉም እኛ ኢትዮጵያውያን እንደ እነዚህ ዓይነት መሰል ውስብስብና ከባድ ችግሮች ሲገጥሙን ይህ የመጀመርያችን አይደለም፤ ቀደም ሲል ከውስጥም ከውጭም  ችግሮች የገጠሙን ወቅት በነበረን አገራዊና ህዝባዊ  ፍቅር፣ በነበረን መደማመጥና መግባባት፣ ሚሊዮኖች እንደ አንድ ሆነን፣  አንዱ እንደሚሊዮን ሆኖ ችግሮቹን እና ፈተናዎችን ተሻግረን  ዛሬ ላይ መድረሳችን በቂ ማሳያ ነው ሲሉ የአንድነት ጥንካሬያችንን አስታውሰዋል::