Articles

የመሀል ሜዳ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል መደበኛ የሕክምና አገልግሎት እየሰጠ ይገኛል።" የሆስፒታሉ ሥራ አስኪያጅ አቶ ወርቅነህ ዘዉዴ 

Mehal Meda

በአሸባሪውና ዘራፊው ቡድን የሕክምና አገልግሎት ያቋረጠው የመሀል ሜዳ ሆስፒታል በዳግማዊ ሚኒልክ ሆስፒታልና በአካባቢው ማህበረሰብ በተደረገለት ድጋፍ የህክምና አገልግሎት መስጠት መጀመሩን የሆስፒታሉ ሥራ አስኪያጅ አቶ ወርቅነህ ዘዉዴ ተናገሩ።


ሆስፒታሉ በተደረገለት የህክምና መገልገያ መሳሪያዎችና የመድኃኒት አቅርቦት ድጋፍ የእናቶችና የህፃናት ጤና አገልግሎት፣ የድንተኛና ጽኑ ሕሙማን አገልግሎት የተመላላሽ ህክምና አገልግሎት በየእለቱ በአማካይ ከ 150 እስከ 200 ታካሚዎች አገልግሎት እየተሰጠ እንደሚገኝ ገልጸው ሙሉ ለሙሉ ሆስፒታሉን ወደ ስራ ለመመለስ ተጨማሪ ድጋፎች እንደሚያስፈልጉ ሥራ አስኪያጁ ተናግረዋል።


በሆስፒተሉ ሲገለገሉ ያገኘናቸው ወ/ሮ አስካለ ገዛኸኝ እና አቶ በልዩ ካሳዬ ተመላላሽ ህክምና ክትትላቸው በመቋረጡ ከፍተኛ ስጋት እንዳሳደረባቸው ገልጸው ሆስፒታሉ አገልግሎት ጀምሮ በማየታቸው መደሰታቸውን ተናግረዋል።

ጤና ሚኒስቴር ለአማራ ክልል ለወደሙ የጤና ተቋማት  አጋር አካላትን በማስተባበር ከ21 ሚሊየን ብር በላይ  የሚያወጡ የህክክምና ግብአቶችን፣ መድሀኒቶችን፣ አንቡላንሶችን እና የጥሬ ገንዘብ ድጋፍ አስረከበ። 

donation

የጤናማ እናትነት ወር በደሴ ከተማ በተከበረበት ስነስርአት ጤና ሚኒስቴር አጋር አካላትን በማስተባበር ለእናቶች እና ህጻናት ጤና ከፍተኛ እገዛ ማድረግ የሚችሉ ከ21 ሚሊየን ብር በላይ የሚያወጡ የህክምና ግብአቶችን፣ መድሀኒቶችን፣ ሁለት አንቡላንሶችን እና ጥሬ ገንዘብ ድጋፍ አበርክቷል። 


የጤና ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴኤታ ዶ/ር ደረጀ ዱጉማ በርክክቡ ወቅት እንደተናገሩት ወራሪው ሀይል ተቋሞቻችንን ቢያወድምም ጠንካራ መንፈሳችንን እና ህብረታችንን ከቶ ሊሰብር አይቻለውምና ከቀድሞ በበለጠ እጅ ለእጅ ያተያይዘን ተቋሞቻችንን እንገነባለን ሲሉ ተናግረዋል።

ደሴ ኮምፕርሄንሲቭ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ወደ አገልግሎት አሰጣጥ በመመለሱ መደሰታቸውን ተገልጋዮች ገለፁ

Community

በጦርነቱ ምክንያት ከረጅም ጊዜ ቆይታ በኋላ የህክምና አገልግሎት መስጠት በጀመረው የደሴ ኮምፕርሄንሲቭ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ግልጋሎት በማግኘታቸው መደሰታቸውን ነዋሪዎች ገለፁ።


በሆስፒታሉ ሲገለገሉ ያገኘናቸው ወ/ሮ መሬሞ ሙሄ እና አቶ አበበ አብረሀም እንደገለፁት የሆስፒታሉ በሮች ተከፍተው ነጭ ገዋን የለበሱ የጤና ባለሙያዎች በፈገግታ ታካሚዎችን ሲያስተናግዱ በማየታቸው ተደስተዋል።


ህዳር 25/ 2014 ዓ ም በሆስፒታሉ እንድትገኝ ከሀኪሟ ቀጠሮ ተሰጥቷት እንደነበርና በነበረው ጦርነት ምክንያት እንዳላቀረበች የተናገራቸው መሬሞ ያ የስቃይ ጊዜ አልፎ ዛሬ ወደ ሆስፒታሉ በመቅረብ ተመርምራ መድሀኒት ሊታዘዝላት በመቻሉ ከጭንቀት እንደገላገላት መስክራለች።


እህቴን ለማሳከም መጥቼ ተገቢውን አገልግሎት አግኝቼ የራጅ ምርመራ ውጤት እየጠበቅን ነው ያለው አበበ በበኩሉ ለዚህ ብርሀናማ ቀን በመብቃታችን ፈጣሪንና መንግስትን አመሰግናለሁ ብሏል።