Articles

በጦርነት እና በተለያዩ ግጭቶች ምክንያት ጉዳት ለደረሰባቸው ዜጎች የስነ አዕምሮ እና የስነ ልቦና ህክምና  ምላሽ ለመስጠት የሚያስችል በጤና ሚኒስቴርና በሴቶችና ማህበራዊ ጉዳዮች ሚኒስቴር የተዘጋጀ የዘርፈ ብዙ ምላሽ እቅድ ይፋ ተደረገ

ministers

በተለያዩ ክልሎች በጦርነት እና በተፈጠሩ ግጭቶች ለተፈናቀሉና ጉዳት ለደረሰባቸው ዜጎች የተቀናጀ  የስነ አዕምሮ እና የስነ ልቦና ህክምና ምላሽ  በመስጠት እየተደረገ ያለውን ድጋፍ ይበልጥ ለማጠናከርና ፈጣን ለማድረግ የጤና ሚኒስቴር እና የሴቶችና  ማህበራዊ ጉዳዮች ሚኒስቴር በጋራ ያዘጋጁት እቅድ ለባለድርሻ አካላት በኢትዮጵያ የህረተሰብ ጤና ኢንስትቲዩት የህብረተሰብ ጤና አደጋዎች የመልሶ ማቋቋምና ሪዚሊየንስ ዳይሬክተር በሆኑት በዶ/ር ያረጋል ፉፋ ቀርቦ ውይይት ተደርጎበታል።


በቅንጅታዊ  ርብርቡ የስነ አዕምሮ ፣  የስነ ልቦና እና የማህበራዊ ስራዎች እንዲሁም ለተለያዩ ባለድርሻ አካላት ግንዛቤ የመፍጠር ተግባራት እንደሚከናወኑ በእቅዱ የተካተቱ ዝርዝር አላማዎች ያሳያሉ፡፡ 

በ2030 እ.ኤ.አ. በሀገር አቀፍ ደረጃ የቤተሰብ ዕቅድ አገልግሎትን ለማሳካት የሚያግዝ የቃል መግቢያ ሰነድ ይፋ ተደረገ 

family planning

ይህ የቤተሰብ እቅድ 2030 የቃል መግቢያ ሰነድ አለም አቀፋዊ ሲሆን 69 ሀገራት የሚሳተፉበት ነው። 


በመድረኩ ላይ የተገኙት የጤና ሚኒስትር ዶ/ር ሊያ ታደሰ እንደተናገሩት በ2030እ.ኤ.አ የቤተሰብ እቅድ አገልግሎትን በሀገርአቀፍ ደረጃ ለማሳካት በምንገባው  ቃል መሰረት የእናቶችና የህፃናትን ጤና ብሎም የአፍላ ወጣቶችንና የወጣቶችን ስነ-ተዋልዶ ጤና  በማሻሻል የተሻለ ጤናማ ዜጋ በመፍጠሩ ረገድ መንግስት ሰፊ ስራ መስራት እንዳለበት ገልጸዋል:: የሁሉንም ተሳትፎ ባካተተ መልኩ የተዘጋጁት የጤናዉ ፖሊሲ ስትራቴጂዎችና  የማስፈጸሚያ ሰነዶችን ወደ ተግባር የመለወጥ ስራ ላይ ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በቅንጅት መስራት እንደሚያሰፈልግና  በገባነው ስምምነት መሠረት ያሉብንን ተደራራቢ ጫናዎችን በመቋቋም ብሎም በጋራ በጥምረት በመስራት ጤናማ ትውልድን ለመፍጠር እና ጤናማ ሀገርን ለመገንባት ይህ የቃል መግቢያ ሰነድ መዘጋጀቱንና ይፋ መደረጉን ተናግረዋል:: 

ጥራት ያለውን የጤና አገልግሎት ተደራሽ ለማድረግ ባለድርሻ አካላት አጋርነታቸውን እንዲያጠናክሩ ተጠየቀ

universal health coverage day

ሁሉን አቀፍ የጤና አገልግሎት ተደራሽነት ቀን /INTERNATIONAL UNIVERSAL HEALTH COVERAGE COMMEMORATION DAY/ “የጤና ኢንቨስትመንት ለሁሉም" /INVEST IN HEALTH SYSTEMS FOR ALL/ በሚል መሪ ቃል በዓለም ዓቀፍ ደረጃ እየተከበረ ነው፡፡ 


ሁሉን አቀፍ የጤና አገልግሎት ተደራሽነት ቀን ሲከበር አጋር አካላት አጋርነታቸውን በመቀጠል በጦርነት የወደሙ ጤና ተቋማትን መልሶ ለማቋቋምና ለአገልግሎት ብቁ ለማድረግ እንዲሰሩ ጠይቀዋል፡፡