Articles

ተንቀሳቃሽ የጤና ቡድን አገልግሎት ተደራሽ ላልሆኑ የአርብቶ አደር የህብረተሰብ ክፍሎች

jigjiga

ከጥቅምት 19_21/2014 ዓ.ም በሶማል ክልል ጅግጅጋ ከተማ የሚካሄደው የጤናው ዘርፍ ልማት የምክክር ጉባኤ በመጀመሪያ ቀን ውሎ በክልሉ የተለያዩ አካባቢዎች ያሉ የጤና አገልግሎት አሰጣጥ ተሞክሮዎችን ምልከታ በማድረግ ጀምሯል።


በጤና ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴኤታ ዶ/ር ደረጀ ዱጉማ እና በሶማሌ ክልል ጤና ቢሮ  ምክትል ሃላፊ ወ/ሮ ሀዋ ሱሌማን የተመራው ቡድን ከጅግጅጋ ከተማ 55 ኪ.ሜ ርቀት ላይ በምትገኘው ጎልጃኖ ወረዳ መልካዳ ካስ ቀበሌ የመስክ ጉብኝት አካሂዷል።


በጉብኝቱም ተግባራዊ በመደረግ ላይ ያለው የተንቀሳቃሽ የጤና ቡድን አገልግሎት የስራ ተሞክሮ ታይቷል። በሶማሌ ክልል በ29 ቡድኖች የተንቀሳቃሽ የጤና አገልግሎት እየተሰጠ ሲሆን እያንዳንዱ ቡድን ለስድስት ቀበሌዎች አገልግሎት ይሰጣል።

በአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት የጥፋት ቡድኑ ባደረሰው ጉዳት ተፈናቅለው ባህርዳር ለሚገኙ ወገኖችና በክልሉ ውስጥ  ጉዳት ለደረሰባቸው  15 ጤና ጣቢያዎች  ድጋፍ ተደረገ 

Amhara

በጤና ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴአታ ወ/ሮ ሠሐረላ አብዱላሂ የተመራ ከጤና ሚኒስቴር፤ ፌዴራል ሆስፒታሎችና ከተጠሪ ተቋማትና ከግሉ ዘርፍ የተውጣጣ ቡድን በአማራ ክልል በባህርዳር ከተማ በህውሃት የጥፋት ቡድን ባደረሰባቸው ጉዳት ተፈናቅለው ጉዳት የደረሰባቸው ዜጎችን ጎብኝቷል።

 
ቡድኑ ከደሴና ኮምቦልቻ አከባቢ በፀጥታው ችግር ምክንያት ተፋናቅለው በባህርዳር ከተማ በዘንዘልማ የተፈናቃዮች መጠለያ የሚገኙትን የጎበኙ ሲሆን በከተማው አስራ አራት ሺ አምስት መቶ ሃያ ሁለት ሺህ የሚሆኑ ተፈናቃይ ወገኖች እንደሚገኙና በመጠለያ ቦታው አራት ሺ ሁለት መቶ ሃምሳ ሁለት ተፈናቃዮች የሚገኙ መሆኑ ታውቋል፡፡ ለተፈናቀሉ ወገኖች የጤና አገልግሎትን ተደራሽ ለማድረግ የክልሉ ጤና ቢሮ ባለሙያዎችን መድቦ ክሊኒክ የከፈተላቸው ሲሆን ከተፈናቀሉ የጤና ባለሙያዎች እና አጋር ድርጅቶች ጋር በመቀናጀት የህክምና አገልግሎትና የማልኑትሪሽን ችግር ልየታ ስራ እየተሰራ መሆኑን መመልከት ተችለዋል። 

የጡት ካንሰር ግንዛቤ ወር የክብርት ፕሬዚደንት መልዕክት

HE the President

የጥቅምት ወር የጡት ካንሰር ግንዛቤ ወር ነው። የጡት ካንሰር ሴቶችን በከፍተኛ  ደረጃ ያጠቃል። በአገራችን ታካሚዎች ወደ ጤና ተቋም የሚሄዱት ዘግይተው ነው። የሚታዩ ምልክቶችን በጊዜ ለመለየት ቅድመ ምርመራ እንዲደረግ የሚመለከታቸው ሁሉ በቂ ግንዛቤ ሊይዙ ይገባል። ይህ ባለመሆኑ ብዙዎችን አጥተናል።


ከአገራችን የተለያዩ ክፍሎች ለጨረርና ለኪሞ ሕክምና የሚመጡ ሴት ወገኖቻችን መጠለያ ቦታ ስለሌላቸው ለተጨማሪ ችግር ይጋለጣሉ። ችግሩን ለመቅረፍ ለእነዚህ ሕሙማን ማረፍያ ቦታ በማዘገጀት፣  ወደ ሆስፒታል በማመላለስ፣ መድሃኒት ግዢ ላይ በመደገፍ ወዘተ . . . ከሚሠሩ ድርጅቶች መካከል "ፒንክ ሃውዝ" የተባለውን በቅርብ ጎብኝቻለሁ። ይህንንና ተመሳሳይ ተቋሟችን በመደገፍ ሴቶች በጊዜ ከተደረሰበት ሊታከም በሚችል በሽታ እንዳይጎዱ እናድርግ።