Articles

በክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎት የአቅመ ደካሞችን ቤት የማደስ ስራ ተጀመረ 

Dr. Lia Tadesse

የጤና ሚኒስቴር እና ተጠሪ ተቋማት በክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎት የአቅመ ደካሞችን ቤት የማደስ ማስጀመሪያ መርኃ ግብር  ዛሬ በልደታ ክፍለ ከተማ፣ ወረዳ 5 የጤና ሚኒስትር ዶክተር ሊያ ታደሰ አስጀምረዋል።


መርኃ ግብሩ ላይ የጤና ሚኒስትር ዶክተር ሊያ ታደሰ፣ ሚኒስትር ዴኤታ ዶ/ር አየለ ተሾመ እና የተጠሪ ተቋማት የስራ ኃላፊዎች እና ሌሎች የሥራ ኃላፊዎችና ሰራተኞች ተገኝተዋል።


ጤና ሚኒስቴርና ከተጠሪ ተቋማት ጋር በመሆን በዘንድሮው መርሐግብር 12 አቅመ ደካሞችን በአዲስ አበባ እና 5 ቤቶችን በክልሎች የሚገነቡ ሲሆን ይህም የእርስ በእርስ የመደጋገፍ ባህልን የሚያዳብርና ለመጪው ትውልድም መልካም እሴትን የሚያሸጋግር ታላቅ በጎ ስራ ነው ብለዋል ሚኒስትር ዶ/ር ሊያ ታደሰ፡፡

ለትግራይ ክልል በአለም አቀፍ ድርጅቶች በኩል አስፈላጊ የህክምና መድሃኒቶችን የማድረሱ እንቅስቃሴ እንደቀጠለ ነው

 supplies

የኢትዮጵያ መንግስት ከሚሰራቸው ቀዳሚ ተግበራት መካከል የጤና አገልግትን ለሁሉም ዜጎች ማድረስ አንደኛው ሲሆን በኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ ህገ መንግስትም እያንዳንዱ ዜጋ የጤና አገልግሎት የማግኘት ጉዳይን በግልጽ ተጠቅሷል፡፡


ስለሆነም ዜጎች  የጤና አገልግሎት በፍትኃዊነት የማግኘት መብት ተግባራዊ ለማድረግ የሚያስችሉ የፖሊሲ አቅጣጫዎች በኢፊዲሪ የጤና ፖሊሲ ተካተዋል፡፡


ከዚህ አኳያ በአገራችን በተከሰቱ ግጭቶች ምክንያት ዜጎች የጤና አገልግሎቶችን የማግኘት ሰብዓዊና  ህገ መንግስታዊ መብቶች እንዳይስተጓጎሉ የኢትዮጵያ መንግስት በተለያዩ ጊዜያት ከአለም አቀፍ አጋር ድርጅቶች ጋር በመሆን ለጤና አገልግሎት አስላፈጊ የሆኑ ድጋፎችን የማድረስ ተግበራትን  አከናውኗል፣ እያከናወነም ይገኛል፡፡

የጤና ሚኒስቴር ''አሻራችን ለትውልዳችን፣ አረንጓዴ ተክላችን ለጤንነታችን!" በሚል መሪ ቃል የችግኝ ተከላ ማስጀመሪያ በኢትዮጵያ የአካል ድጋፍ አገልግሎት ማዕከል ተከናወነ።

Dr. Lia Tadesse

በዛሬው ዕለት የችግኝ ተከላ ማስጀመሪያ መርሐ ግብር በኢትዮጵያ የአካል ድጋፍ አገልግሎት (በገፈርሳ የአዕምሮ ህሙማን ማገገሚያ ማዕከል) የተከናወነ ሲሆን በ2014 ዓ.ም ክረምት ወራት የጤና ሚኒስቴርና ተጠሪ ተቋማት  ከ50 ሺ በላይ ችግኞችን ለመትከል ወደ ተግባር መግባቱን የጤና ሚኒሰቴር ሚኒስትር ዶ/ር ሊያ ታደሰ ተናግረዋል።


በኢትዮጵያ የአካል ድጋፍ አገልግሎት (በገፈርሳ የአዕምሮ ህሙማን ማገገሚያ ማዕከል 20  ሺህ ለምግብነት የሚውሉ ችግኞች የመትከሉ መርሀ ግብር የተከናወነ ሲሆን በተጨማሪም በማእከሉ የተከናወኑ የልማት እና የማስፋፊያ ስራዎች የወተት ልማትን ጨምሮ የከተማ ግብርናን የመተግበር ስራ እንዲሁም የህክምና አገልግሎት አሰጣጥ ተጎብኝተዋል። ይህም ተግባር በማዕከሉ ያለውን የምግብ አቅርቦት በራስ አቅም ለመሸፈን ያስችላል ተብለዋል።