Articles

የኤች.አይ.ቪ/ኤድስ መከላከል እና መቆጣጠር የ2015 እቅድ ማስተዋወቂያ እና የምክክር መድረክ ተካሄደ

Hiwot Solomon

የዘንድሮው አመታዊ አገራዊ የኤች.አይ.ቪ/ኤድስ መከላከል እና መቆጣጠር እቅድ የክልል እና ከተማ መስተዳድር ጤና ቢሮዎችን እና ኤች.አይ.ቪ/ኤድስ መከላከል እና መቆጣጠር ጽህፈት ቤቶችን ሴክተር መስሪያ ቤቶችን እንዲሁም ሌሎች ባለድርሻ አካላትን በማስተባበር የተዘጋጀ ሲሆን፤ የ2014 በጀት አመት አፈጻጸምን በመገምገም 2015 በጀት አመት እቅድ ዝግጅት የጋራ ለማድረግና ቀጣይ እርምጃዎችን ለማፋጠን ይረዳ ዘንድ የተዘጋጀ የምክክር መድረክ መሆኑን በጤና ሚኒስቴር የበሽታዎች መከላከልና መቆጣጠር ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር ወ/ሮ ህይወት ሰለሞን ገልጸዋል፡፡

በተለያዩ አካላት ሲመራ የነበረው የኤች.አይ.ቪ/ኤድስ መከላከል እና መቆጣጠር ስራ አዲስ በተቀመጠው አቅጣጫ መሰረት በአንድ እንዲመራ መደረጉ መልካም ነው ያሉት ዳይሬክተሯ፤ በአለም አቀፍ ደረጃ የተቀመጠውን አቅጣጫ በማሳካት የኤች.አይ.ቪ/ኤድስ ስርጭትን በ2030 ለማስቆም መስራት ይገባል ብለዋል፡፡

የኮቪድ 19 ወረርሽኝን በመከላከልና በመቆጣጠር ረገድ ሚና ለነበራቸው የቅዱስ ጳውሎስ ሆስፒታል ሚሊኒየም ሕክምና ኮሌጅ ባለሙያዎች የምስጋና መርሀግብር ተካሄደ።

St Paul

በቅዱስ ጳውሎስ ሆስፒታል ሚሊኒየም ሕክምና ኮሌጅ በተዘጋጀዉ ፕሮግራም ላይ የተገኙት የጤና ሚኒስቴር ሚኒስትር ዶ/ር ሊያ ታደሰ ባደረጉት ንግግር በሀገራችን ባለፉት ጊዜያት በተከሰቱ የኮቪድ 19 ወረርሽኝ እና ጦርነት በቀዳሚነት ምላሽ በመስጠት ላበረከቱት አስተዋጽዖ አመስግነዋል። የቅዱስ ጳውሎስ ሆስፒታል ሚሊኒየም ኮሌጅ አመራሮች እና ሰራተኞች በዛ አስቸጋሪ ወቅት ዋጋ ከፍለው ላሳዩት ርብርብ ሚኒስቴር መስሪያቤቱ እውቅና እና ምስጋና ያቀርባል ብለዋል።


በዚያ ወረርሽኝ ወቅት የሆስፒታሉ አመራሮች እና ሰራተኞች ቅድሚያ ተነሳሽነት በማሳደር በሚሊኒየም የኮቪድ ማእከል መስዋትነት በመክፈል ጭምር ለሰሩት ስራ እና በሌሎች ክልሎችም ማእከላቱ እንዲስፋፉ በማገዝ ላበረከታችሁት አስተዋጽዎ ምስጋና ይገባችዃል ያሉት ዶክተር ሊያ ትልቅ ስራ እና ሀላፊነትም መወጣት የሚችል አቅም እንዳለን የተገነዘብንበትና የኮራንበት ስራም ነው ብለዋል።

የኢትዮጵያ የውስጥ ደዌ ህክምና ማህበር 7ኛው ዓመታዊ ሳይንሳዊ ጉባኤ ተካሄደ

group picture

በእለቱ በክብር እንግድነት የተገኙት የጤና ሚኒስትር ዴኤታ ዶክተር አየለ ተሾመ በጉባኤው መክፈቻ ላይ ባደረጉት ንግግር እንደገለጹት ባለፉት ሁለት አስርት አመታት የኢትዮጵያ ጤና ፖሊሲ በማህበረሰብ ጤና ማጎልበት፣ በሽታ መከላከልና የጤና አገልግሎት ሽፋን ማሻሻል ላይ ትኩረት አደርጎ የተሰራበት እና በዚህም ብዙ ስኬቶች  የተመዘገቡበት እንደነበር የተናገሩ ሲሆን በአሁኑ ወቅት ግን የተላላፊ በሽታዎች ብቻ ሳይሆኑ ተላላፊ ያልሆኑ በሽታዎች እና አደጋዎችም በከፍተኛ ሁኔታ መጨመራቸውን ተከትሎ የከፍተኛ የፈውስ ህክምና ፍላጎትም እንዲሁ የጨመረበት ወቅት በመሆኑ የጤና ሚኒስቴር ለዚሁ ምላሽ በሁሉም የአገሪቱ ክፍሎች የሶስተኛ ደረጃ /tertiary care/  አገልግሎት ተደራሽነትንና ጥራትን ለማሻሻል እየሰራ እንደሚገኝ ተናግረዋል፡፡