Articles

መድሃኒት የተላመደ የቲቢ በሽታ ከተስፋፋባቸው 33 ሀገራት ዝርዝር ውስጥ ኢትዮጵያ መውጣቷ መልካም አጋጣሚ ነዉ።

Dr. Lia Tadesse

ኢትዮጵያ ዓለም አቀፍ መድሃኒት የተላመደ የቲቢ በሽታን መግታት የድርጊት መርሃ ግብር ተቀብላ እየሰራች ነዉ ያሉት የጤና ሚኒስቴር ሚንስትር ዶ/ር ሊያ ታደሰ ናቸው፡፡ ክብርት ሚኒስትሯ ይህንን ያሉት በምስራቅ መካከለኛና ደቡብ አፍሪቃ (ECSA) ዓመታዊ የቲቢ በሽታ ምርመራ ላብራቶር የማጠናከሪያ ውይይት መድረክ ላይ ነዉ። በአገራችን በቲቢ መከላከል ዙሪያ የተሰሩ ስራዎች አበረታች ለውጥ እያሳዩ መሆኑን የገለጹት ሚኒስትሯ በዋቢነትም በዓለም መድሃኒት የተላመደ የቲቢ በሽታ ከተስፋፋባቸው 33 ሀገራት ዝርዝር ውስጥ ኢትዮጵያ መውጣቷ መልካም አጋጣሚ እንደሆነ ገልጸዋል።


የECSA ዳይሬክተር ጀኔራል ፕ/ር ዮስዋ ደምብስያ እንደተናገሩት የአፍሪካ ችግሮች ለአፍሪካኖች እንዲፈቱ አስታውሰው በግሎባል ፈንድ የቲቢ ላብራቶር ምርመራ ማጠናከሪያ ኘሮጀክት ላለፉት ሰባት ዓመታት ሲያግዙ ለቆዩ ባለድርሻ አካላት ምስጋና አቅርበው ለወደፊትም ይህ ሥራ ተጠናክሮ እንዲቀጥል ድጋፋቸው እንደሚያስፈልግ ጠቁመዋል፡፡

ጳጉሜ 1 የበጎ ፈቃደኝነት ቀን አስመልክቶ የጤና ሚኒስቴር፣  የትምህርት ሚኒስቴር እና የስራና ክህሎት ሚኒስቴር በጋራ የሚያዘግጁት የሙሉ ቀን መርሃ ግብር በሚኒሊክ አጠቃላይ ሁለተኛ ደረጃ እና የመጀመርያ ደረጃ ትምህርት ቤት በተለያዩ ዝግጅቶች ተጀምሯል።

Dr. Lia Tadesse

ዛሬ ጳጉሜ 1 የበጎ ፈቃደኝነት ቀን በማስመልከት በአራዳ ክፍለ ከተማ በሚኒሊክ አጠቃላይ ሁለተኛ ደረጃ እና የመጀመርያ ደረጃ ትምህርት ቤት የትምህርት ተቋማትን ፅዱና ውብ በማድረግ እንደዚሁም የተተከሉ ችግኞችን በማረም ፣ በመኮትኮት እና በመንከባከብ መርሃ ግብር  ተጀምሯል።

በማስጀመሪያ መርሀ ግብሩ ላይ የጤና ሚኒስትር ዶ/ር ሊያ ታደሰ፣ የትምህርት ሚኒስትር ፕሮፌስር ብርሃኑ ነጋ እና ሌሎች ጥሪ የተደረገላቸዉ እንግዶች ተገኝተዋል፡፡

መርሀ ግብሩ ለ2015 ዓ.ም የትምህርት ዘመን የትምህርት ተቋማት ለተማሪዎች ምቹ ፣ ፅዱ፣ ውብና ማራኪ እንዲሁም ሳቢ እንዲሆኑ እና ለመማር ማስተማሩ ሂደት ጉልህ ሚና እንዲኖራቸው ለማድረግ የሚያስችል ነው።

ጳጉሜ 1 የበጎ ፈቃደኝነት ቀን በተለያዩ መርሀ ግብሮች የሚቀጥል ይሆናል።

"ድህረ ጦርነትና የአጥንት ህክምና" በሚል መሪ ቃል 16ኛ የኢትዮጵያ የአጥንት ህክምና ሃኪሞች ማህበር አመታዊ ጉባኤ በአዲስ አበባ ተካሄደ

Dr. Ayele Teshome

በጉባዔው ላይ በክብር እንግድነት ተገኝተው ንግግር ያደረጉት የጤና ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴኤታ ዶ/ር አየለ ተሾመ የማህበሩ አባላት በግለሰብም ደረጃም ሆነ እንደ ተቋም ሃገር በተቸገረችበት ጊዜ ሁሉ በሰው ሰራሽና ተፈጥሮአዊ አደጋዎች በተለይም በጦርነት ጉዳት ለሚደርስባቸው የኢትዮጵያ ጀግና ሰራዊት አባላትን ህይወት ለመታደግ ላበረከቱት እና እያበረከቱት ያለው አገልግሎት በታሪክ መዝገብ ላይ መፃፉን ጠቅሰው ለአበርክቶዓቸው ሁሉ ኢትዮጵያ ታመሰግናለች ብለዋል።