Articles

እኤአ በ2030 የቲቢ በሽታን ለመግታት ቀጣይነት ባለዉ የልማት ግብ የተያዘዉ ዕቅድን ለማሳካት ተገቢዉን ትኩረት ሳያገኝ የቆየዉ የህጻናትና አፍላ ወጣቶች የቲቢ በሽታ ልይታ፣ ምርመራና ህክምና ላይ ትኩረት በማድረግ መስራት  ያስፈልጋል።

Dr. Lia Tadesse

የኢፌድሪ ጤና ሚኒስትር ክብርት ዶ/ር ሊያ ታደሰ በሎሜ ቶጎ እየተካሄደ ባለዉ 72 ኛው የአፍርካ አህጉር የአለም ጤና ድርጅት መድረክ ላይ እንደገለጹት በኢትዮጵያ በ2015 የጸደቀዉ የህጻናትና አፍላ ወጣቶች የቲቢ በሽታ ፍኖተ ካርታ ተግባራዊ መሆን ከጀመረ ወዲህ ህጻናትና አፍላ ወጣቶችን ከቲቢ በሽታ የመከላከልና ህክምና ስራ መሻሻሉን ተናግረዋል።  


በኢትዮጵያ በተሰራዉ ስራ በበሽታዉ የሚያዙና የሚሞቱ ሰዎች ቁጥር  ቢቀንስም የቲቢ በሸታ እንዲሁም የቲቢ -ኤች አይቪ ጫና አሁንም ከፍተኛ በሆነባቸዉ 30 አገሮች አንዷ መሆኗን ያወሱት ዶ/ር ሊያ፣ የቲቢ በሽታን ለመከላከልና ለመቆጣጠር የሚሰሩ ስራዎች ለቲቢ ይበልጥ ተጋላጭ የሆኑና የተዘነጉ የህብረተሰብ ክፍሎች ላይ ትኩረት ማድረግ ይገባል ብለዋል።

“በጎነት ለጤናችን’’በሚል ነፃ የጤና ምርመራ እና የህክምና የበጎ ፍቃድ አገልግሎት በክልሎችና በከተማ መስተዳደሮች ተጠናክሮ ቀጥሏል፡፡

voluntary service

በአገር አቀፍ ደረጃ በአንድ ሳምንት ከመቶ ሺ በላይ ለሚሆኑ ዜጎች የነጻ የጤና ምርመራ እና ህክምና አገልግለት ለመስጠት የተጀመረው  ሰው- ተኮር የበጎ ፈቃድ የተግባር ዘመቻ  በሁሉም ክልሎችና በከተማ መስተዳደሮች በተጠናከረ መልኩ ቀጥሏል፡፡


በዘመቻውም የጤና አጠባበቅ ትምህርትና ምክር አገልግሎት ፣ በተላላፊና ተላላፊ ያልሆኑ በሽታዎች ፣የኮሌራና ሌሎች ውሀ ወለድ በሽታዎች፣ ወባ፣ ኤች አይ ቪ ፣ ቲቪ ፣ ኮቪድ-19፣ የካንሰር ህመምና ሌሎች ትኩረት በሚሹ የጤና ጉዳዮች ላይ ማለትም የደም ግፊት ፣የደም የስኳር መጠን፣ ከአንገት በላይ፣ የአይን፣ የቆዳ፣የስነ ምግብ፣ የአእምሮ ጤና  እና ሌሎች የጤና አገልግሎቶች እየተሰጡ ይገኛሉ፡፡

የኢትዮጵያ ልዑካን ቡድን በ72 ኛው የአፍርካ አህጉር የአለም ጤና ድርጅት መድረክ ላይ እየተሳተፈ ነው።

Dr. Dereje Duguma

ዛሬ በሎሜ ቶጎ የተጀመረዉ 72 ኛው የአፍርካ አህጉር የአለም ጤና ድርጅት መድረክ ላይ የኢትዮጵያ ልዑካን ቡድን እየተሳተፈ ይገኛል።  

                         
ይህ 72 ኛው የአፍሪከ አህጉር ከዓለም ጤና ድርጅት ስድስት የአህጉራዊ አስተዳደር አካላት አንዱ ሲሆን 47 አባል ሀገራት ያሉት  የአፍሪካ ክልል ሀገራት የሚወክሉበት  ኮሚቴ ነው፡፡ 


በመድረኩም የአፍርካ የአለም ጤና ንኡስ ኮሚቴዎች እባላት የሚሰየም ሲሆን እኤአ የ2022 የስራ እፈጻጸም እንዲሁም የአፍሪካ ማህበረሰብ ጤና አሁናዊና ቀጣይ  ስትራቴጅክ ጉዳዮች ከአለማችን ማህበረሰብ ጤና ጋር ያለዉ አጠቃላይ ሁኔታ በመድረኩ ቀርበው ምክክርና ውይይት የሚደረግ ይሆናል። 


መድረኩም ለቀጠይ 5 ቀናት በሎሜ ቶጎ የሚቀጥል ይሆናል።