የኢትዮጵያ ልዑካን ቡድን በ72 ኛው የአፍርካ አህጉር የአለም ጤና ድርጅት መድረክ ላይ እየተሳተፈ ነው።

  • Time to read less than 1 minute
Dr. Dereje Duguma

ዛሬ በሎሜ ቶጎ የተጀመረዉ 72 ኛው የአፍርካ አህጉር የአለም ጤና ድርጅት መድረክ ላይ የኢትዮጵያ ልዑካን ቡድን እየተሳተፈ ይገኛል።  

                         
ይህ 72 ኛው የአፍሪከ አህጉር ከዓለም ጤና ድርጅት ስድስት የአህጉራዊ አስተዳደር አካላት አንዱ ሲሆን 47 አባል ሀገራት ያሉት  የአፍሪካ ክልል ሀገራት የሚወክሉበት  ኮሚቴ ነው፡፡ 


በመድረኩም የአፍርካ የአለም ጤና ንኡስ ኮሚቴዎች እባላት የሚሰየም ሲሆን እኤአ የ2022 የስራ እፈጻጸም እንዲሁም የአፍሪካ ማህበረሰብ ጤና አሁናዊና ቀጣይ  ስትራቴጅክ ጉዳዮች ከአለማችን ማህበረሰብ ጤና ጋር ያለዉ አጠቃላይ ሁኔታ በመድረኩ ቀርበው ምክክርና ውይይት የሚደረግ ይሆናል። 


መድረኩም ለቀጠይ 5 ቀናት በሎሜ ቶጎ የሚቀጥል ይሆናል።