የአፍሪካ የሕክምና ትምህርት (MedEDAfrica 2026) ኮንፈረንስ በስኬት ተጠናቀቀ!

MedEDAfrica 2026

በኢትዮጵያ አስተናጋጅነት በአዲስ አበባ ለሦስት ቀናት ሲካሄድ የቆየው የአፍሪካን የሕክምና ትምህርት ማዘመን ላይ ያተኮረው የ"MedEDAfrica 2026" ዓለም አቀፍ ኮንፈረንስ ዛሬ ተጠናቋል። 


በመዝጊያ ሥነ ሥርዓቱ የጤና ሚኒስትር ዴኤታ ወ/ሮ ሳህረላ አብዱላሂ የሕክምና ትምህርትን ማጠናከርና የጤና ባለሙያዎችን አቅም መገንባት የጤና አገልግሎት ጥራትና ደህንነትን ለማሻሻል ወሳኝ መሆኑን ገልጸው፣ ኢትዮጵያም የሥልጠና ጥራትንና የባለሙያዎችን ተደራሽነት ለማሳደግ በርካታ ተግባራትን እያከናወነች መሆኑን አስታውሰዋል።


ወ/ሮ ሳህረላ ኢትዮጵያ የጤና ባለሙያዎችን ቁጥር፣ ተደራሽነትና የሥልጠና ጥራት ለማሳደግ የተለያዩ ፕሮግራሞችን በመተግበር የጤና ሥርዓቱን እያጠናከረች መሆኑን ገልጸው፣ ከዚህ በተጨማሪም የጎረቤት ሀገራት የሕክምና ተማሪዎችን በሬዚደንሲ ፕሮግራም በማሰልጠን የክልሉን የጤና ሰው ኃይል ልማት እየደገፈች መሆኑን አስታውቀዋል።

"ጠንካራ የመጀመሪያ ደረጃ የጤና ክብካቤ ሥርዓቶችን ለመገንባት ዲጂታል ጤናን ጥቅም ላይ ማዋል" በሚል መሪ ሃሳብ ሶስተኛው የምስራቅ እና ደቡብ አፍሪካ ሃገራት የጤና መሪዎች የምክክር መድረክ በአዲስ አበባ መካሄድ ጀመረ 

Consultation Forum

ሦስተኛው ዓመታዊ አውደ ጥናት፤ በምሥራቅና ደቡብ አፍሪካ የሚገኙ ከፍተኛ የጤና፣ የገንዘብ እና  የኢንፎርሜሽንና የኮሙኒኬሽን ቴክኖሎጂ (ICT) ባለሥልጣናትን በመሰብሰብ አገራዊ ትብብርን ለማጠናከርና የጋራ የመማማሪያ መረብ ለመፍጠር ያለመ ነው። 


የአውደ ጥናቱ ዋና ዓላማ ይበልጥ ፍትሃዊ፣ ጠንካራ እና በበጀት ረገድ ዘላቂነት ያለው የመጀመሪያ ደረጃ የጤና ሥርዓት ለመገንባት የሚያስችል የጋራ ቀጠናዊ የዲጂታል ጤና ራዕይን ማምጣት መሆኑን ያስረዱት የጤና ሚኒስትር ዶ/ር መቅደስ ዳባ ናቸው።


 ተሳታፊዎቹ በየአገራቱ ያለውን ተሞክሮ፣ የአፈጻጸም ማነቆዎችን እና የዲጂታል ጤና መፍትሔዎችን በሰፊው ተግባራዊ ለማድረግ የተገኙ ትምህርቶችን ይለዋወጣሉ፤ እንዲሁም ቴክኖሎጂ የጤና የሰው ኃይል አስተዳደርን እና የመረጃ ውህደትን እንዴት እንደሚያሳድግ ያላቸውን ቴክኒካዊ ግንዛቤ ያሳድጋሉ ሲሉ ሚኒስትሯ ተናግረዋል። 

የአፍሪካ የሕክምና ትምህርት «MedEDAfrica 2026» አህጉራዊ ጉባኤ በአዲስ አበባ መካሄድ ጀመረ

MedEDAfrica 2026

ኢትዮጵያ በሕክምና ትምህርትና በዲጂታል ፈጠራ የአህጉራችንን የነገ ተስፋ ለመቅረጽ በቁርጠኝነት እየሠራች እንደምትገኝ የገለፁት ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ክቡር አቶ ተመስገን ጥሩነህ ናቸው።

ሀገራችን ከራሷ አልፋ ከአፍሪካ ሀገራት የመጡ የጤና ባለሞያዎችን በከፍተኛ የሕክምና ትምህርት ተቋሞቿ በማስተማር እንደ ቀጣናዊ የልቀት ማዕከል እያገለገለች ትገኛለች ያሉት ክቡር አቶ ተመስገን፣ በክቡር ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አሕመድ መሪነት ሀገራችን በሰው ሠራሽ አስተውሎት እና በዲጂታል ፈጠራ የአህጉሪቱ ተምሳሌት ለመሆን ራሷን እያዘጋጀችም ነው ብለዋል። 

በአፍሪካ አህጉራችን ውስጥ የሚገኙ ዩኒቨርሲቲዎቻችን፣ ሆስፒታሎቻችን እና የኢንዱስትሪው ዘርፍ በጋራ ሊሠሩ፣ የምርምር ውጤቶችም የፖሊሲ መመሪያ ሊሆኑና የሕዝቡን ሕይወት በተግባር ሊለውጡ ይገባል ብለዋል ክቡር አቶ ተመስገን።

የጤና ሚኒስትር ዶ/ር መቅደስ ዳባ ከአሜሪካ ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ምክትል ረዳት ጸሐፊ ዶ/ር ማማዲ ይላ ጋር በመንግስት ለመንግስት  የሚሰሩ የጤና ጉዳዮች ዙሪያ ተወያዩ

Dr Mekdes Daba

የጤና ሚኒስትር ዶ/ር መቅደስ ዳባ፣ የኢትዮጵያ እና የአሜሪካ መንግስታት በጤናዉ ዘርፍ ዘርፈብዙ የትብብር ስራዎችን ለረጅም ግዜ በጋራ እያከናወኑ መሆኑን ገልጸዉ በተለይም  የዲጂታል ጤና አገልግሎትን በማስፋፋት፣ የወባ ወረርሽኝን በመከላከል፣ የእናቶችና ህጻናትን ጤና በመጠበቅ እንዲሁም የቲቢ እና የኤች.አይ.ቪ/ኤድስ ስርጭትን በመግታት ረገድ ዉጤቶች መገኘቱን ተናግረዋል።


​በቀጣይም የመጀመሪያ ደረጃ የጤና ክብካቤ አገልግሎትን  በማጎልበት ጠንካራ የጤና ስርዓትን ለመፍጠር  ዘላቂ የጤና ልማት ግቦችን ሙሉ በሙሉ ለማሳካት ኢትዮጵያ እያደረገች ያለዉን ጥረት አሜሪካ እያደረገች ያለዉን ድጋፍ  አጠናክራ እንድትቀጥል ጠይቀዋል። 

በስዊዘርላንድ ጄኔቫ እየተካሄደ ባለዉ የዓለም ጤና ጉባኤ የጎንዮሽ መድረኮች በተለያዩ የጤና ርዕሰ ጉዳዮች ላይ ዉይይት ተካሂዷል

#WHA79

በስዊዘርላንድ ጄኔቫ እየተካሄደ ባለዉ የዓለም ጤና ጉባኤ የጎንዮሽ መድረኮች የኢትዮጵያ ልዑካን ቡድን በተገኙበት በተለያዩ ጤና ርዕሰ ጉዳዮች ላይ ዉይይት ተካሂዷል።

ኢትዮጵያ ከሩዋንዳ፣ ጊኒ፣ ኔፓል፣ እና አጋር አካላት ጋር በትብብር ባዘጋጀችዉ የጎንዮሽ መድረክ የድንገተኛ፣ ቀዶጥገና ህክምና አገልግሎትን በተመለከተ የጤና ሚኒስትር ዶ/ር መቅደስ ዳባ የኢትዮጵያን ተሞክሮ ባጋሩት ገለጻ ታካሚን ማእክል ያደረገ የድንገተኛ ቀዶጥገና ህክምና አገልግሎት ማጠናከርና ተደራሽ ማድረግ ሁለንተናዊ የጤና ሽፋንና የጤና ዋስትናን ለማረጋገጥ በጣም አስፈላጊ መሆኑን ተናግረዋል።

ኢትዮጵያና ባርቤዶስ በጤናው ዘርፍ በጋራ ለመስራት የሚያስችላቸውን ስምምነት ተፈራረሙ

#WHA79

ኢትዮጵያና ባርቤዶስ በካሪኮም የትብብር ማእቀፍ በቀጠናው ባሉ ሀገራት መካከል በትብብር ለመስራት በሁለቱ ሀገራት መሪዎች በተደረሰዉ ስምምነት መሰረት እና ማእቀፍ መነሻ በማድረግ የተለያዩ ስራዎች እየተሰሩ ይገኛል።


የዚሁ ትብብር መስክ አካል የሆነ በጄኒቫ እየተካሄደ ከሚገኘው የዓለም የጤና ጉባኤ #WHA79 ጎን ለጎን በጤናው ዘርፍ በጋራ ለመስራት የሚያስችል ስምምነት በሁለቱ ሀገራት የጤና ሚኒስትሮች የተፈረመ ሲሆን ስምምነቱ በዋናነት በሀገራቱ መካከል የአቅም ግንባታ እና ክህሎት ሽግግር፤ የባለሙያዎች ትብብርና በተለያዩ የጤና ጉዳዮች ላይ በትብብር ለመስራት ታሳቢ ያደረገ ሲሆን በተጨማሪም በሁለቱ ሀገራት መካከል ያለውን የህዝብ ለህዝብ ግንኙነት ለማጠናከር እንደሚረዳም ይታመናል።

79ኛዉ የዓለም ጤና ጉባኤ በስዊዘርላንድ ጄኔቫ እየተካሄደ ይገኛል

WHA79


በጤና ሚኒስትር ዶ/ር መቅደስ ዳባ የተመራዉ የኢትዮጵያ ልዑካን ቡድን በጄኔቫ እየተካሄደ በለዉ 79ኛዉ የዓለም ጤና ጉባኤ ላይ እየተሳተፈ ይገኛል።


በጉባኤዉ ላይ ንግግር ያደረጉት የጤና ሚኒስትር ዶ/ር መቅደስ ዳባ በቅርቡ ይፋ የሆነዉ የህብረተሰብ ጤና ዳሰሳ ጥናት ግኝት መሰረት ኢትዮጵያ የእናቶችና ህጻናት ሞትን በመቀነስ ረገድ አመርቂ ዉጤት ማስመዝገቧን በመግለጽ በቀጣይም አለም አቀፍ የጤና ተደራሽነትን በማረጋገጥ ለመጀመሪያ ደረጃ ጤና ክብካቤ ከፍተኛ ትኩረት ተሰጥቶ ጠንካራ የጤና ስርዓት እንዲፈጠር በትጋት እንደሚሰራ አጽንኦት በመስጠት ተናግረዋል። 

ኢትዮጵያ እንደ ዓለም ጤና ጉባኤ ያሉ አለም አቀፍ መድረኮችን በመጠቀም የጤና ዲፕሎማሲን በማጠናከር ላይ ትገኛለች - የጤና ሚኒስትር ዶ/ር መቅደስ ዳባ 

WHA79

በጤና ሚኒስትር ዶ/ር መቅደስ ዳባ የተመራዉ የኢትዮጵያ ልዑክ ቡድን በ79 ነኛዉ የዓለም ጤና ጉባኤ ላይ ለመሳተፍ ስዊዘርላንድ ጄኔቫ ገብቷል።


ዶ/ር መቅደስ ለልዑካን ቡድኑ ኦሪየንቴሽን በሰጡት መድረክ እንደገለጹት ኢትዮጵያ በተለይም እንደ የዓለም ጤና ጉባኤ ያሉ አለም አቀፍ መድረኮችን በመጠቀም የጤና ዲፕሎማሲን በማጠናከር ላይ ትገኛለች ብለዋል። 


ኢትዮጵያ የዓለም ጤና ድርጅት አባል ሀገር እንደመሆኗ በጉባኤዉ በሚወሰኑ ዉሳኔዎችና ቀጣይ ስራዎች የራሷን ድርሻ እንደምትወጣ ዶ/ር መቅደስ ተናግረዋል።


ወቅታዊ የኢቦላና ሀንታ ቫይረስ ሁኔታን ጨምሮ ሌሎች የዓለማችን ስጋት የሆኑ ወርሽኞችን መከላከልና መቆጣጠር በዋናነት በጉባኤዉ ቀርበዉ ዉይይት እንደሚደረግበት ይጠበቃል።

የዲጂታል ጤና ዘርፍ መሪ (Champion) በመሆን የተሰጣቸዉን ኃላፊነት አስመልክቶ የአፍሪካ በሽታ መቆጣጠሪያ እና መከላከያ ማዕከል (Africa CDC) ዋና ዳይሬክተር ከሆኑት ከዶክተር ዣን ካሴያ ጋር ዉጤታማ  ውይይት አድርገዋል 

AI

በውይይታቸዉም በተለያዩ ቅድሚያ የሚሰጣቸው ጉዳዮች ላይ የመከሩ ሲሆን፤ በተለይም በአፍሪካ ሕብረት የሰው ሰራሽ አስተውሎት (AI) እና የዲጂታል ጤና ዘርፍ መሪ (Champion) በመሆን የተሰጣቸዉን አዲስ ኃላፊነት በሚመለከት በስፋት ተነጋግረዋል።


የፈጠራ ሥራዎች ለአፍሪካ ዕድገት ምንጊዜም ወሳኝ መሰረት ናቸዉ ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐብይ አህመድ በጤናው ዘርፍ የሚገጥመንን ተለዋዋጭ ተግዳሮቶች ለመወጣት የሰው ሰራሽ አስተውሎትንና የዲጂታል ቴክኖሎጂዎችን ዐቅም መጠቀም የጤና ሥርዓታችንን ለማጠናከር፣ ተደራሽነትን ለማስፋፋት እና ለሕዝባችን የተሻለ ውጤት ለማስመዝገብ ወሳኝ ነው ብለዋል።