በጤና ሚኒስቴር እና ግብርና ሚኒስቴር የሚመራ የዓለም ጤና ድርጅት የምግብና የእርሻ ድርጅትን እንዲሁም ዩኒሴፍን ያካተተው ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች ቡድን በዛሬው እለት በኦሮሚያ ክልል በድርቅ የተጎዳዉን የቦረና ዞንን ጎብኝቷል። 

Borena

በዱቡሉቅ ወረዳ የዱቡሉቅ ጤና ጣቢያ አጣዳፊ የምግብ እጥረት ህክምና መስጫ ማዕከልንና የመጠጥ ውሃ ጥራት ቁጥጥርን እንዲሁም በድርቁ የተጎዱ የማህበረሰብ ክፍሎችን ቡድኑ ተመልክቷል። 


በጉብኝቱም ቡድኑ ከዞኑ አመራሮች ጋር በወቅታዊዉ ሁኔታና የድንገተኛ ድጋፍ አሰጣጥን አስመልክቶ ውይይት ያደረገ ሲሆን በድርቁ የተጎዱ እና የጤና እና የምግብ እጥረት ጉዳት የደረሰባቸዉን ዜጎች ለማከም፤ ለመደገፍ የሚዉሉ ከአለም ጤና ድርጅት የተገኙ 31 ሜትሪክ ቶን የድንገተኛ ህክምና ቁሳቁስ ድጋፎችንም አበርክቷል።


በቀጣይም ክፍተት ባለባቸው ላይ የፌደራል መንግስትና አጋር አካላትና ድጋፉን አጠናክረው እንደሚቀጥሉ ገልጸዋል።

በፌደራል ጤና ሚኒስቴር እና ግብርና ሚኒስቴር የሚመራ የዓለም ጤና ድርጅት የምግብና የእርሻ ድርጅትን ያካተተ ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች ቡድን በድርቅ የተጎዳዉን የሱማሌ ክልል ሸበሌ ዞንን ጎብኝቷል።

Somali

የጎዴ አጠቃላይ ሆስፒታል የምግብ እጥረት ህክምና መስጫ ማዕከልን፣ ፈጣን ምላሽ ህክምና አሰጣጥን እንዲሁም በጎዴ ወረዳ የክትባት፣ የስነ ምግብ፣ የመጠጥ ውሃ አቅርቦት ድጋፍ፣ የእንስሳት ምገባ ድጋፍ አገልግሎት ለማህበረሰቡ በፌደራል በክልልና በአጋር ድርጅቶች ቅንጅት እየተሰጠ የሚገኝበትን ሁኔታም ተመልክቷል።


ከጉብኝቱ በተጨማሪም ቡድኑ ከክልሉ ፕሬዝዳንት ክቡር አቶ ሙስጤፌ መሃመድ እና ከሌሎች የክልሉ ሃላፊዎች ጋር በድርቅ የተጎዱ ቦታዎችን ምላሽ አሰጣጥና ድጋፍ ዙሪያ ውይይት አድርጓል። 

በኢትዮጵያ ሁለተኛ የሆነው የካንሰር ህክምና ጨረር አገልግሎት መስጫ ማዕከል ተመረቀ

Inauguration

በኢትዮጵያ በየአመቱ ከሰባ ሺ በላይ ዜጎች በተለያየ አይነት የካንሰር በሽታዎች እንደሚጠቁ ጥናቶች ያሳያሉ፡፡ ለእነዚህ የማህበረሰብ ክፍሎች የጨረር ህክምና አገልግሎት ሲሰጥ የቆየው የጥቁር አንበሳ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ብቻ ነበር፡፡


በዛሬው ዕለት የተመረቀውና አገልግሎት እየሰጠ የሚገኘው የጅማ ዩንቨርስቲ ሆስፒታል የጨረር ህክምና ማዕከል በከፍተኛ ወጪ መዘጋጀቱና አገልግሎት መጀመሩ በጥቁር አንበሳ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ላይ ብቻ ተወስኖ የቆየው የጨረር ህክምና አገልግሎት ጫናን በመቀነስ በህክምናው ተደራሽነት ላይ ትልቅ አስተዋጽኦ ያደርጋል ተብሏል፡፡

ሰማሪታንስ ፐርስ ኢንተርናሽናል ሪልፍ የእርዳታ ድርጅት ለኢትዮጵያ 12.5 ሚሊዮን ብር የሚገመት የህክምና ቁሳቁስና ግብአት ድጋፍ አደረገ

Samaritan’s Purse

የጤና ሚኒስትር ዶ/ር ሊያ ታደሰ በቦሌ አየር ማረፊያ ተገኝተው ከሰማሪታንስ ፐርስ ኢንተርናሽናል ሪልፍ ካንትሪ ዳይሬክተር ሪል ላን ድጋፉን ተረክበዋል፡፡ ዶ/ር ሊያ በርክክብ ስነስርዓቱ ጊዜ እንደተናገሩት መቀመጫውን በአሜሪካ አገር ያደረገው የሰማሪታንስ ፐርስ ኢንተርናሽናል ሪልፍ በኢትዮጵያ ከንጹህ የመጠጥ ውኃ አቅርቦትና ሳኒቴሽን፣ ከኮቪድ-19 እና በሌሎች የድንገተኛ ምላሽ ድጋፍ ስራዎችን ሲሰራ የቆየ ተቋም መሆኑን አንስተው አሁን 12.5 ሚሊዮን ብር የሚያወጡ የህክምና ግብአትና መሳሪያዎች ድጋፍ ማድረጉን ገልጸዋል፡፡ 

በውጭ ሀገር ከሚኖሩ ኢትዮጵያውያን እና ትውልደ አትዮጵያውያ የተሰባሰቡ መድኃኒቶች ጥቃት ለተፈጸመባቸው የህክምና ተቋማት ማሰራጨት ተጀመረ።

Donation

የጤና ሚኒስቴር ከዲያስፖራው ማህበረሰብ የተደረጉ ድጋፎችን በተቀናጀ መልኩ እንዲሰበሰብ፣ እንዲለይና በጦርነቱ ለተጎዱ ጤና ተቋማት ከተደለደለ በኋላ ስርጭቱ እንዲከናወን በተሰጠው አቅጣጫ መሰረት የኢትዮጵያ መድኃኒት አቅራቢ አገልግሎት ለየጤና ተቋማቱ ከየካቲት 04/2014 ዓ.ም ጀምሮ ስርጭት እያከናወነ ሲሆን  እስካሁንም ሸዋሮቢት፣ በአጣዮ ሆስፒታል እና ጤና ጣቢያ፣ በከሚሴ ሆስፒታል፣ በኮንቦልቻ ሆስፒታል እና ጤና ጣቢያ፣ በደሴ ሆስፒታል፣ በሰኞ ገበያ ጤና ጣቢያ፣ እና በቦሩ ሜዳ ሆስፒታል ድጋፉን ማድረስ ተችሏል። በመቀጠልም አፋር ክልልን ጨምሮ በተቀሩ አከባቢዎች የሚሰራጭ ይሆናል።

የአውሮፓ ህብረት አባል አገራት ለኢትዮጵያ የኮቪድ-19 ክትባት ድጋፍ አደርጉ!

EU

ኢትዮጵያ የኮቪድ-19 ክትባት ድጋፍ ከአውሮፓ ህብረት አገራት ተረከበች። 


ድጋፍ ያደረጉ አገራት ሰድስት ሲሆኑ እነሱም ፈርንሳይ (6746 400)፣ ፊላንድ(1699200) ዴንማርክ (1560000)፣ ግሪክ (1346400) ጣልያን (1264110 ) ስዊድን (480690) ዶዝሰ በአጠቃላይ (13 096 800 ዶዝስ) የኮቪድ-19 ክትባት ድጋፍ ማግኘቷ ታውቀዋል። 


በርክክብ ስነስርኣቱ የአገራቱ አምባሳደሮች፣ የኢምባሲ ተወካዮች፣ የዩኒሴፍ ተጠሪዎች የተገኙት ሲሆን የጤና ሚኒስትር ዶክተር ሊያ ታደሰ ጋር ውይይት አድርገዋል፡፡ 
በመድረኩ ላይ ዶክተር ሊያ እንዳሉት የተደረገው ድጋፍ የክትባት አቅርቦትን እንደሚያሳድግ ገልጸው ይህም ለበሽታው መግታትና መከላከል ትልቅ ፋይዳ እንደሚኖረው ተናግረዋል። 

የኢትዬጵያ ሕብረተሠብ ጤና ኢንስቲትዩት ለኢ.ፌ.ዴ.ሪ ሀገር መከላከያ ሰራዊት 5 ሚሊዮን ብር እና ከ200 ሺ ብር በላይ የሚገመት አልባሳት ድጋፍ ተደረገ

Defense Force

በርክክቡ ወቅት የጤና ሚኒስቴር ዶ/ር ሊያ ታደሰ ባስተላለፉት መልእክት የኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊት ለሀገር ህልውና እና እያደረገ ያለው አስተዋጽኦ ከፍተኛ መሆኑን ገልፀው የኢትዮጵያ ሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት ይህን ታሳቢ በማድረግ ያደረገውን ድጋፍ አመስግነዋል። ይህም ድጋፍ 5 ሚሊዬን ብር እና ከ200 ሺ በላይ የሚገመቱ አንሶላዎች፣ ቢጃማና ነጠላ ጫማዎች መሆኑንም ገልፀዋል።

የመከላከያ ሠራዊት ምንስትር ዴኤታ ወ/ሮ ማርታ ሊዊጂ በበኩላቸው የጤናው ዘርፍ በዚህ ፈታኝ ወቅት ለሀገር እያደረገ ያለው አበርክቶ እጅግ ከፍተኛ መሆኑን ገልፀው አሁንም በገንዘብና በዓይነት በኢትዬጵያ ሕብረተሠብ ጤና ኢንስቲትዩት የመጣው ድጋፍ ለመከላከያ ሠራዊት የሚሰጠው አገልግሎት እጅግ ከፍተኛ መሆኑን በመግለጽ በመከላከያ ሰራዊት ስም አመስግነዋል።

የጤና ሚኒስቴር በአለታ ወንዶ ከተማ በአነስተኛ የኑሮ ደረጃ ለሚገኙ አባወራዎች ያስገነባቸው  ቤቶችን ለተጠቃሚዎች አስረከበ 

Aleta Wondo

የጤና ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴኤታ ዶ/ር ደረጀ ዱጉማ በክረምት በጎ አገልግሎት በአለታ ወንዶ ከተማ በዝቅተኛ ኑሮ ለሚገኙ ስድስት አባወራዎች/እማወራዎች ያስገነባቸውን ቤቶች ለተጠቃሚዎች ያስረከቡ ሲሆን በክረምት በጎ አገልግሎት የጤና ሚኒስቴር ችግኞችን የመትከል እና አቅመ ደካሞችን የማገዝ ስራን ሲሰራ እንደነበር አስታውሰው በአለታ ወንዶ ከተማም ምሳሌ መሆን የሚችል ስራ መሰራቱን ተናግረዋል። ቤቶቹም መሰረታዊ መገልገያ ቁሳቁስ የተሟላላቸው ሲሆን ድጋፉ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል አረጋግጠዋል። 


ድጋፍ የተደረገላቸው ግለሰቦችም በሰጡት አስተያየት መጠለያ ማጣት እጅግ አስቸጋሪ ህይወት እንዲመሩ እንደዳረጋቸው ሆኖም ጤና ሚኒስቴር  እንደደረሰላቸው እና ተስፋቸውን እንዳለመለመ ገልጸው ምስጋናቸውን አቅርበዋል። 

አዳዲስ ምሩቃን ሃኪሞችን ወጪን በመጋራት  ወደ ስራ ለማስገባት ከጥቂት ሳምንታት በፊት ይፋ የተደረገውን ፕሮጀክት አስመልክቶ ምክክር ተደርገ

HR

ጤና ተቋማት ያለባቸውን የሰው ሃይል እጥረት ለማቃለል እና ለተመራቂ ሃኪሞች የስራ እድል ለመፍጠር ይፋ የተደረገውን የ3 ዓመት ፕሮጀክት ስራ በተመለከተ ወርክሾፕ ተካሂደዋል።


ጤና ሚኒስቴር ከአጋር ድርጅቶች እና ክልል ጤና ቢሮዎች ጋር በመሆን ወጪን  በመጋራት አዳዲስ ሃኪሞችን ወደ ስራ ለማስገባት በተጀመረው ፕሮጀክት መሰረት እየሰራ መሆኑን የተናገሩት በጤና ሚኒስቴር የሰው ሀብት አስተዳደር ዳይሬክተር አቶ ሀብታሙ ደምሴ በፕሮጀክቱ ከ2011 ጀምሮ ተመርቀው ያልተቀጠሩ 2898 ሃኪሞችን ወደ ስራ ለማስገባት የሚያስችል የበጀት ዝግጅት መጠናቀቁን ገልጸዋል፡፡

ትኩረት የሚሹ የሀሩራማ በሽታዎችን ለመከላከል እና ለመቆጣጠር ሁሉም ባለድርሻ አካላት በጋራ በመቀናጀት መስራት ይገባል

NTD

በሲዳማ ክልል አስተናጋጅነት በሀገራችን ለሶስተኛ ጊዜ እየተዘከረ ባለው የአለም ትኩረት የሚሹ የሀሩራማ በሽታዎች ቀንን አስመልክቶ የጤና ሚኒስትር ዴኤታ ዶ/ር ደረጀ ዱጉማ ባስተላለፉት መልእክት እንደ ዝሆኔ/ፖዶኮኒዮሲስ፣ ሊንፋቲክ ፊላሪያሲስ፣ ሀይድሮ ሲል፣ ሌሽሚያሲስ የመሳሰሉ የቆላማ እና ሀሩራማ በሽታዎች ለረጅም ዘመን ትኩረት ሳያገኙ በመቆየታቸው ዜጎችን ለተለያዩ አካላዊ፣ ስነ-ልቦናዊ፣ ማህበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ ጉዳቶች እየዳረጉ መሆናቸውን ተናግረው ይህንን ለመቀየር ጥራት ያለው የጤና አገልግሎትን በሁሉም ስፍራ ማዳረስ ረገድ ሁሉም በጤና ዘርፍ እየሰሩ ያሉ አካላት ተገቢ ትኩረት እንዲሰጡ፣ እንዲሁም በጋራ በመቀናጀት እንዲሰሩ ጥሪ አቅርበዋል።