በከፍተኛ ወጪ ተገንብተው አገልግሎት ሲሰጡ የነበሩ  የደሴና የኮምቦልቻ ጤና ተቋማት በአሸባሪውና ወራሪው የህውሃት ቡድን አገልግሎት እንዳይሰጡ ሆነው ወድመዋል፡፡      

health facility

በደሴ ከተማ የሚገኘው የደሴ አጠቃላይ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል በአሸባሪውና ወራሪው የህውሀት ቡድን አገልግሎት እንዳይሰጥ ሆኖ የወደመ ሲሆን ቡድን በተደራጀ መልኩ የህክምና መሳሪያዎችንና ሌሎች አስፈላጊ ግብዓቶችን ጭኖ ከመውሰዱ ባለፈ የቀሩትንም ጥቅም ላይ እንዳይውሉ አድርጎ ሙሉ በሙሉ አውድሟቸዋል።


ከእነዚህም መካከል በተኝቶ ህክምና፣ በፅኑ ህክምናና በአንስተኛና በከፍተኛ የቀዶ ህክምና ክፍሎች የነበሩ በብዙ ሚሊዮን ብር የተገዙ የትንፋሽ መስጫ /ventilator/ እና አንስቴዥያ ማሽኖች የተወሰዱ ሲሆን ቀሪዎቹ ደግሞ ሙሉ በሙሉ በመውደማቸው በአሁኑ ወቅት ሆስፒታሉ አገልግሎት መስጠት በማይችልበት ደረጃ ላይ ይገኛል።

የጤና ሚኒስቴር ለሀገር መከላከያ ሰራዊት 30 ሚሊዮን ብር እና 1.5 ሚልዮን ብር የሚገመቱ የተለያዩ የዓይነት ድጋፎችን አደረገ

donation

በድጋፍ ርክክቡ ላይ የጤና ሚኒስትር ዶ/ር ሊያ ታደሰ  እንደተናገሩት አሁን ላይ አገራችን እና ህዝቦቿ ከመቼውም በተለየ ከውስጥም ከውጪም ፈተናዎች  እና መሰናክሎች የገጠሟት ወቅት ላይ እንደምንገኝ ገልጸው በሁሉም መስኮች በማህበራዊ ፣ በፖለቲካዊ፣ በኢኮኖሚያዊ እና በውጭ ጉዳዮቻን ላይ የገጠሙን ችግሮች ለጊዜው ሊፈትኑን እና ሊከብዱን ቢችሉም እኛ ኢትዮጵያውያን እንደ እነዚህ ዓይነት መሰል ውስብስብና ከባድ ችግሮች ሲገጥሙን ይህ የመጀመርያችን አይደለም፤ ቀደም ሲል ከውስጥም ከውጭም  ችግሮች የገጠሙን ወቅት በነበረን አገራዊና ህዝባዊ  ፍቅር፣ በነበረን መደማመጥና መግባባት፣ ሚሊዮኖች እንደ አንድ ሆነን፣  አንዱ እንደሚሊዮን ሆኖ ችግሮቹን እና ፈተናዎችን ተሻግረን  ዛሬ ላይ መድረሳችን በቂ ማሳያ ነው ሲሉ የአንድነት ጥንካሬያችንን አስታውሰዋል::

የኮቪድ-19 የክትባት ዘመቻ ሊካሄድ ነው!

covid19

ጤና ሚኒስቴር ከመምህራት ማህበር ጋር በመሆን የኮቪድ-19 የክትባት ዘመቻ ውጤታማ በሚሆንበት  መንገድ ዙሪያ በአዳማ እየመከረ ነው፡፡  


የፀጥታ ችግር በሌለባቸው የአገራችን ክፍሎች ከ12 ሚሊዮን በላይ ዶዝ ለመከተብ የታሰብ ሲሆን በተለይም በትምህርት ቤት እና በዩኒቨርስቲዎች ተደራሽ ለማድረግ አስፈላጊው ዝግጅት መደረጉን የጤና ሚኒስቴር የክትባት ባለሙያ አቶ ተመስገን ለማ ተናግረዋል፡፡


በክትባት ዘመቻው እድሚያቸው ከ18 አመት በላይ የሆነ ማንኛው ሰው እና በመንግስት እና በግል ትምህርት ቤቶች የሚያስተምሩ መምህራንን የመከተብ ስራ እንደሚሰራ በመድረኩ ተገልፃል፡፡


ከኮቪድ-19 የክትባት ዘመቻ በተጨማሪ በቀጣይም የማህፀን በር ካንሰር ክትባት በመንግስት እና በግል ትምህርት ቤቶች እድሚያቸው ከ14 አመት ለሆናቸው ልጃገራዶች ክትባቱን ለመስጠት የዘመቻ ስራ እንደሚጀመር አቶ ተመስገን ለማ ጠቁመዋል፡፡

በጅግጅጋ ከተማ በተካሄደው 23ኛ የጤናው ዘርፍ ጉባኤ ተሳታፊ የነበሩ ሁሉም ታዳሚዎች የኮቪድ 19 ምርመራ እንደተደረገላቸው ተገለጸ።

RDT test

ይህም በርካታ ቁጥር ያለው ተሳታፊ ለሚገኝባቸው ወሳኝ  ሀገራዊ ሁነቶች  ምሳሌ የሚሆን ተግባር መሆኑ ተነግሯል። 
"ፈጣን ምላሽ ሰጪ የጤና ስርአት በአዲስ ምእራፍ" በሚል መሪ ቃል  የሱማሌ ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት መዲና በሆነችው ጅግጅጋ  ሲካሄድ የሰነበተው የጤናው ዘርፍ ጉባኤ ሁሉም ተሳታፊዎች ከጉባኤው  አንድ ቀን አስቀድሞ የኮቪድ 19 ምርመራ የወሰዱበትና ከቫይረሱ ነጻ መሆናቸው የተረጋገጠ ተሳታፊዎች የተገኙበት እንዲሁም ሌሎችም  ሁሉም የጥንቃቄ መንገዶች የተተገበሩበት እንደሆነ ገልጸው  ለሌሎች ተመሳሳይ ሀገራዊ ሁነቶች ትምህርት የሰጠ እንደነበር ተሳታፊዎች ተናግረዋል። 

የጤና ሚኒስቴር በአዲስ መልክ ያበለፀገውን ዌብ ሳይት ይፋ አደረገ

website

አዲሱ ዌብ ሳይት ሁለገብና መረጃዎችን በተደራጀና ሳቢ በሆነ መንገድ ለተጠቃሚዎችና ለባለድርሻ አካላት የሚያደርስ መሆኑን የገለፁት ዌብ ሳይቱ እውን መሆኑን ያስተዋወቁት በጤና ሚኒስቴር የሚኒስትሯ ከፍተኛ አማካሪ ዶ/ር ዳንዔል ገብረሚካኤል ናቸው።


የቀድሞው ዌብ ሳይት መረጃ እንደልብ የማይገኝበትና ሳቢ እንዳልነበረ ቅሬታ የሚቀርብበት ነበር ያሉት ዶ/ር ዳንዔል አዲሱ ዌብ ሳይት በተገቢ መረጃዎች የተደራጀና ለአጠቃቀም ሳቢ እና ቀላል ሆኖ የቀረበ ሲሆን ማንኛውም  ከሀገር ዉጪም ሆነ በሀገር ውስጥ ለሚገኙ ተገልጋዮች የኢ ላይብረሪ ፣ኦን ላይን የበጎ ፈቃድና ልገሳ አገልግሎት፣ የአስተያየት/ቅሬታ ማቅረቢያ፣ የቴሌቪዥን ቻናል፣ የዲጂታል ጤና ሲስተሞች፡ የጤና ማህበራት የጥናትና ምርምር ውጤቶችን እና ሌሎችንም ያካተተ መሆኑ ተገለጿል።

በጅግጅጋ ከተማ የተካሄደው 23ኛው የጤና ዘርፍ ጉባኤ የ2014 ዓ.ም ዕቅድን በጋራ ለማሳካት የሚያስችል የቃል ኪዳን ስምምነት ከክልሎችና ከተማ መስተዳድሮች ጋር በመፈራረም ተጠናቋል

final

"ምላሽ ሰጪ የጤና ስርዓት በአዲስ ምዕራፍ " በሚል መሪ ቃል ለሶስት ቀናት በጅግጅጋ ከተማ ሲከናወን የቆየው 23ኛው የጤናው ዘርፍ ዓመታዊ ጉባዔ ተጠናቋል።


በጉባኤው ማጠናቀቂያ ላይ የጤና ሚኒስትር ዶ/ር ሊያ ታደሰ ከዘጠኝ የክልልና ሁለት የከተማ መስተዳድር የጤና ቢሮ ኃላፊዎች ጋር ባደረጉት ስምምነት መሠረት በበጀት ዓመቱ የተቀመጡ ዕቅዶችን በጋራ ለማሳካት የሚያስችሉ ግብዓቶችን በማሟላትና የተቀናጀ ርብርብ በማድረግ ለህብረተሰቡ ተገቢውንና ጥራት ያለውን የጤና አገልግሎትፍትሃዊና ተገልጋይ ተኮር በሆነ መልኩ ለማቅረብ በስምምነት ፊርማቸው በጋራ ቃል ገብተዋል።


ጉባዔውን በንግግር የዘጉት የጤና ሚኒስቴር ሚኒስትር ዶ/ር ሊያ ታደሰ ጉባኤው በተሳካ ሁኔታ እንዲከናወን ያደረጉትን አጋር አከላት እና በተለይም የሶማሌ ክልልን ካመሰገኑ በኋላ ሁላችንም በያለንበት ለህብረተሰቡ ሁሉን አቀፍ የጤና አገልግሎት ለማዳረስ ተግተን መስራት ይገባናል ብለዋል።

ጠንካራ የፋይናንስና ፍትሃዊ የጤና ስርዓቶች ጥራት ላለው የጤና አገልግሎት

discussion

በጅግጅጋ በሚካሄደው የጤናው ዘርፍ ልማት ጉባኤ የሁለተኛ ቀን ውሎ ተሳታፊዎች በተለያዩ ጤና ጉዳዮች ላይ የፓናል ውይይት አካሂደዋል፡፡
የጤና ሚኒስትር ዶ/ር ሊያ ታደሠ እና የጤና ሚኒስትር ዴኤታ ወ/ሮ ሰሃረላ አብዱላሂ የተገኙበት የፓናል ውይይት የጤና ፋይናንስን እና ፍትሃዊነትን ማሻሻል ላይ ትኩረት ያደረገ ነበር፡፡


የጤና ፋይናንስ ስርዓቱን አስመልክቶ በቀረበው ፓናል ውይይት ከሃገር አቀፍና ከዓለም አቀፍ ድርጅቶች የሃብት ማሰባሰብ ስራዎች የተሰሩ ሲሆን መንግስት ከጠቅላላው በጀት ውስጥ 13 ነጥብ 2 በመቶ የሚሆነውን ለጤናው ዘርፍ እንዲመደብ ለማድረግ ተችሏል፡፡  
የግሉን የጤና ዘርፍና የመንግስትን ትብብር ለማጠናከር በተሰራው ስራ የግሉ ዘርፍ ተሳትፎ በተለይም የጤና ግብአቶች ምርትና ተርሸሪ ኬር ላይ እንዲጨምር ማድረግ መቻሉ በውይይቱ ተነስቷል፡፡ 

በጂግጂጋ ዩኒሸርሲቲ ሼህ ሀሰን የቦሬ ሪፈራል ሆሰፒታል የሚገኘው የኩላሊት እጥበት ማእከል እና የጂግጂጋ የደምና ቲሹ ባንክ በዛሬው እለት በጤና ሚኒስቴር ከፍተኛ አመራሮች ተጎብኝቷል

visit

የጤና ሚኒስቴር ከፍተኛ የስራ አመራሮች ከክልሉ የጤና ቢሮ የስራ ኃላፊዎች ጋር በመሆን በሆስፒታሉ የሚገኙ የMRI ክፍልን፣ የኩላሊት እጥበት ህክምና ማእከልን፣ የደምና ቲሹ ባንክን የጎበኙ ሲሆን በተለይ የከተማዋ ህብረተሰብና ባለሀብቶችን በማሳተፍ የተቋቋመው የኩላሊት እጥበት ህክምና ማእከል አገልግሎት አሰጣጥ ተዘዋዉረው ተመልክተዋል።


የኩላሊት እጥበት ህክምና ማእከሉ ከሱማሌ ና ከአካባቢው ለሚመጡ ተካሚዎች በተመጣጣኝ ዋጋ አገልግሎት ተደራሸ እያደረገ እንደሆነ በጉብኝቱ ተገልጿል። በዚህም በ2013 ዓ.ም ለ724 ታካሚዎች አገልግሎቱን መስጠት  እንደተቻለ ተገልጿል።


በተለይ የጂግጂጋ የደምና ቲሹ ባንክ የመረጃ ስርአቱን ዲጂታላይዝ የማድረግ ስራን ዶ/ር ሊያ ታደሰ በጉኝቱ ወቅት በይፋ ያሰጀመሩ ሲሆን የምርመራ ሂደቱን በአዉቶሜሸን በመታገዝ እየተከናወነ እንደሚገኝ ተመልክተዋል። 

ተንቀሳቃሽ የጤና ቡድን አገልግሎት ተደራሽ ላልሆኑ የአርብቶ አደር የህብረተሰብ ክፍሎች

jigjiga

ከጥቅምት 19_21/2014 ዓ.ም በሶማል ክልል ጅግጅጋ ከተማ የሚካሄደው የጤናው ዘርፍ ልማት የምክክር ጉባኤ በመጀመሪያ ቀን ውሎ በክልሉ የተለያዩ አካባቢዎች ያሉ የጤና አገልግሎት አሰጣጥ ተሞክሮዎችን ምልከታ በማድረግ ጀምሯል።


በጤና ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴኤታ ዶ/ር ደረጀ ዱጉማ እና በሶማሌ ክልል ጤና ቢሮ  ምክትል ሃላፊ ወ/ሮ ሀዋ ሱሌማን የተመራው ቡድን ከጅግጅጋ ከተማ 55 ኪ.ሜ ርቀት ላይ በምትገኘው ጎልጃኖ ወረዳ መልካዳ ካስ ቀበሌ የመስክ ጉብኝት አካሂዷል።


በጉብኝቱም ተግባራዊ በመደረግ ላይ ያለው የተንቀሳቃሽ የጤና ቡድን አገልግሎት የስራ ተሞክሮ ታይቷል። በሶማሌ ክልል በ29 ቡድኖች የተንቀሳቃሽ የጤና አገልግሎት እየተሰጠ ሲሆን እያንዳንዱ ቡድን ለስድስት ቀበሌዎች አገልግሎት ይሰጣል።

በአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት የጥፋት ቡድኑ ባደረሰው ጉዳት ተፈናቅለው ባህርዳር ለሚገኙ ወገኖችና በክልሉ ውስጥ  ጉዳት ለደረሰባቸው  15 ጤና ጣቢያዎች  ድጋፍ ተደረገ 

Amhara

በጤና ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴአታ ወ/ሮ ሠሐረላ አብዱላሂ የተመራ ከጤና ሚኒስቴር፤ ፌዴራል ሆስፒታሎችና ከተጠሪ ተቋማትና ከግሉ ዘርፍ የተውጣጣ ቡድን በአማራ ክልል በባህርዳር ከተማ በህውሃት የጥፋት ቡድን ባደረሰባቸው ጉዳት ተፈናቅለው ጉዳት የደረሰባቸው ዜጎችን ጎብኝቷል።

 
ቡድኑ ከደሴና ኮምቦልቻ አከባቢ በፀጥታው ችግር ምክንያት ተፋናቅለው በባህርዳር ከተማ በዘንዘልማ የተፈናቃዮች መጠለያ የሚገኙትን የጎበኙ ሲሆን በከተማው አስራ አራት ሺ አምስት መቶ ሃያ ሁለት ሺህ የሚሆኑ ተፈናቃይ ወገኖች እንደሚገኙና በመጠለያ ቦታው አራት ሺ ሁለት መቶ ሃምሳ ሁለት ተፈናቃዮች የሚገኙ መሆኑ ታውቋል፡፡ ለተፈናቀሉ ወገኖች የጤና አገልግሎትን ተደራሽ ለማድረግ የክልሉ ጤና ቢሮ ባለሙያዎችን መድቦ ክሊኒክ የከፈተላቸው ሲሆን ከተፈናቀሉ የጤና ባለሙያዎች እና አጋር ድርጅቶች ጋር በመቀናጀት የህክምና አገልግሎትና የማልኑትሪሽን ችግር ልየታ ስራ እየተሰራ መሆኑን መመልከት ተችለዋል።