የኮቪድ-19 የክትባት ዘመቻ ሊካሄድ ነው!

  • Time to read less than 1 minute
covid19

ጤና ሚኒስቴር ከመምህራት ማህበር ጋር በመሆን የኮቪድ-19 የክትባት ዘመቻ ውጤታማ በሚሆንበት  መንገድ ዙሪያ በአዳማ እየመከረ ነው፡፡  


የፀጥታ ችግር በሌለባቸው የአገራችን ክፍሎች ከ12 ሚሊዮን በላይ ዶዝ ለመከተብ የታሰብ ሲሆን በተለይም በትምህርት ቤት እና በዩኒቨርስቲዎች ተደራሽ ለማድረግ አስፈላጊው ዝግጅት መደረጉን የጤና ሚኒስቴር የክትባት ባለሙያ አቶ ተመስገን ለማ ተናግረዋል፡፡


በክትባት ዘመቻው እድሚያቸው ከ18 አመት በላይ የሆነ ማንኛው ሰው እና በመንግስት እና በግል ትምህርት ቤቶች የሚያስተምሩ መምህራንን የመከተብ ስራ እንደሚሰራ በመድረኩ ተገልፃል፡፡


ከኮቪድ-19 የክትባት ዘመቻ በተጨማሪ በቀጣይም የማህፀን በር ካንሰር ክትባት በመንግስት እና በግል ትምህርት ቤቶች እድሚያቸው ከ14 አመት ለሆናቸው ልጃገራዶች ክትባቱን ለመስጠት የዘመቻ ስራ እንደሚጀመር አቶ ተመስገን ለማ ጠቁመዋል፡፡


ዘመቻው ውጤታማ እንዲሆን የትምህርት ዘርፉ አጋርነት ትልቅ ድርሻ እንዳለው በመድረኩ ተነስቷል፡፡