የቀዶ ህክምና፣ የድንገተኛና ጽኑ ህክምና አገልግሎት ጥራትንና ተደራሽነትን ለማሻሻል በትኩረት መስራት ያስፈልጋል።

Dr. Ayele Teshome

የጤና ሚኒስቴር ከደብረብርሀን ዩንቨርሲቲ፣ ከስማይል ትሬን (Smile Train) እና ከኬፕ ታውን ዩንቨርሲቲና ጋር በመቀናጀት ለ3 ቀናት በአዲስ አበባ ሲያካሂድ የነበረውን የዓለም የቀዶ ህክምና፣ የድገተኛና ፅኑ ህሙማን ህክምና አገልግሎት የአመራር ክህሎት ዓውደ ርዕይ ተጠናቋል፡፡ 


በጥናታዊ ዓውደ ርዕዩ የማጠቃለያ መርሐ ግብሩ ላይ የተገኙት የጤና ሚንስቴር ሚንስትር ዲኤታ ዶ/ር አየለ ተሾመ እንደተናገሩት አውደ ርዕዩ በዓለም አቀፍ የቀዶ ሕክምናና የድንገተኛና ጸኑ ህክምና ላይ ትኩረት አድርጎ መወያየቱ የሚደገፍና ትክክለኛው ጊዜ መሆኑን ጠቅሰው እንደ ሃገር የአገልግሎቱን ጥራትና ተደራሽነት ለማስፋፋት የጤና ሚኒስቴር በ5 ዓመቱ እስራቴጂክ ዕቅድ አካቶ በትኩረት እየሰራ መሆኑን አስታውቀዋል፡፡

በኢትዮጵያና በአጎራባች ሀገራት የጤና ስርዓትን  ለማጠናከር የሚያግዙ ስምምነቶችና እርዳታዎች ተደረጉ፡፡

Agreements

የሀገራችን የጤና ስርዓትን በማጠናከር የሀገር ውስጥና ድንበር ተሻጋሪ የጤና በሽታዎችን ለመከላከልና ለመቆጣጠር የበለጠ ተግቶ መስራት እንዲቻል በዛሬው እለት በኢትዮጵያ የሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት በአውሮፓ ህብረት ድጋፍና በምስራቅ አፍሪካ በየነ-መንግስታት ድርጅት (ኢጋድ)እንዲሁም በዩኖፕስ አስተባባሪነት የኢትዮጵያንና የአጎራባች ሀገራት የጤና ስርዓትና የኮቪድ-19 ምላሽን ለመደገፍ ለኢትዮጵያ የጤና ሚኒስቴር በተደረገው ልዩ ልዩ የጤና አምቡላንሶችና ቁሳቁሶች ርክክብ እና የመግባቢያ ሠነድ ፊርማ ሥነ-ሥርዓት ላይ የጤና ሚኒስትር ክብርት ዶ/ር ሊያ ታደሰ እንደገለጹት የተሻለ ጤናን መኖር የሚቻለው የተሻለ የጤና ሥርዓት ሲገነባ እንደሆነ በአጽንኦት ተናግረዋል፡፡

በጤና ኤክስቴንሽን መርሃ-ግብር ትግበራ የአጋር ድርጅቶች ሚና ውጤታማ ነበር

Health Extension

በጤና ኤክስቴንሽን መርሃ-ግብር ትግበራ በርካታ የጤና አገልግሎቶች ማህበረሰቡን ተደራሸ ለማድረግ የአጋር ድርጅቶች ሚና ውጤታማ እንደነበር እና እንደ ሃገር አመርቂ የጤና ውጤቶች የተመዘገበበት እንደሆነ ተጠቁሟል፡፡ 


በፕሮግራሙ  ላይ ተገኝተው ንግግር ያደረጉት የጤና ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴኤታ ዶ/ር ደረጄ ድጉማ እንደገለጹት የጤና ስርዓታችን በተለይም የእናቶችና ህጻናት ጤና አገልግሎትና የመጀመሪያ ደረጃ የጤና አገልግሎት ተጠቃሚ የሆነበት የጄ ኤስ አይ/ኤል10ኬ 10 ኪሎ ሜትር/JSI L10K 10K/ ባለፉት 14 ዓመታት የነበረው አገልግሎት ውጤታማ እንደነበር አንስተው ከጤና ሚኒስቴር ጋር በቅንጅት በመስራት ለተገኘው ውጤትና ድጋፍ ላደረጉ አካላት ምስጋናቸውን አቅርበው። በቀጣይም ይህ ፕሮጅክት ቀጣይነት እንዲኖረው ድጋፍ የሚያደርጉ አካላት በትብብር ውጤታማ ስራ ለመስራት ድጋፋቸውን አጠናክረው እንዲቀጥሉ ጥሪያቸውን አስተላልፈዋል፡፡   

"በግሎባል ፈንድ የሚተገበሩ ፕሮግራሞች ውጤት ተኮር በመሆናቸው ሁሉም አካል በትኩረት ሊሰራባቸው ይገባል።" የጤና ሚኒስትር ዴኤታ - ዶ/ር ደረጀ ዱጉማ

Dr. Dereje Duguma

ግሎባል ፉንድ ግራንት ፕሮግራም ትግበራ ሂደቶችን የመገምገም እና እስካሁን በተያዙ እቅዶች አፈጻጸም ላይ ያተኮረ ግምገማ  ዛሬ በጤና ሚኒስቴር መሰብሰቢያ አዳራሽ ተካሂዷል፡፡ 


የግምገማ መድረኩ በጤና ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴኤታ ዶ/ር ደረጄ ዱጉማ የተመራ ሲሆን ትኩረቱንም እስካሁን ባለፉት ዘጠኝ ወራት ከግሎባል ፈንድ በተገኝው የፋይናንስ ድጋፍ በጤናው ዘረፍ የተከናወኑ ዝርዝር ስራዎች ቀድሞ ከታቀደው እቅድ አኳያ አሁናዊ ደረጃው ምን እንደሚመስል እና የእቅድ አተገባበሩ ምን ደረጃ ላይ እንደሚገኝ የተገመገመበት ነው።


የጤና ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴኤታ ዶ/ር ደረጄ ዱጉማ በግምገማ መድረኩ እንደተናገሩት በግሎባል ፈንድ የሚተገበሩ ፕሮጀክቶች ውጤት ተኮር በመሆናቸው ሁሉም አካል በትኩረት ሊሰራባቸው እንደሚገባ  አንስተዋል፡፡ 

የኮቪድ-19 መከላከያ ክትባት ተደራሽነትን ለማሳደግ ከአጋር ድርጅት ኃላፊዎችና ተወካዮች ጋር ውይይት ተደረገ

Discussion

የኮቪድ-19 መከላከያ ክትባት ተደራሽነትና ሽፋንን አስመልክቶ በጤና ሚኒስቴር በየደረጃው የሚገኙ ኃላፊዎች፣የጋቪ፣ የዩኒሲኤፍ እና የአለም ጤና ድርጅት ተወካዮችና ኃላፊዎች በተገኙበት ውይይት ተደረጓል፡፡ 


ባለፉ በርካታ ዓመታት የክትባት አገልግሎት ተደራሽነት ላይ በቁርጠንነት ድጋፍ ሲያደርጉ የቆዩ አጋር ድርጅቶችን በማመስገን ንግግራችውን የጀመሩት የጤና ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴኤታ ዶ/ር ደረጄ ዱጉማ ሲሆኑ በተለይ የኮቪድ ወረርሽኝን ከመግታትና አፋጣኝ ምላሽ ከመስጠት ረገድ ባለድርሻ አካላት የነበራቸው ሚና ከፍተኛ ነበር ብለዋል፡፡

የ2021 የአለም አቀፍ የምግብ እጥረት ጠቋሚ በኢትዮጵያ ይፋ ሆነ

Global Hunger Index

የምግብ እጥረት ጠቋሚ በኢትዮጵያ ይፋ ይተደረገው ‹‹ግጭት ባለባቸው ቦታዎች የምግብ አቅርቦትን ለማሻሻል በአጋርነት መሥራት›› በሚል መሪ ቃል ነው፡፡ 


የምግብ እጥት ብዙ ችግሮችን የሚያካትት በመሆኑ በትኩረት መሰራት እንዳለበት የጠቆሙት የጤና ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴኤታ ዶ/ር ደረጀ ዱጉማ፤ በ2021 የነበረውን ሂደት በሚያስረዳው ሪፖርት የመክፈቻ ዝግጅት ላይ ባደረጉት ንግግር እንደተናገሩት የኢትዮጵያ መንግስት የምግብና ስነ-ምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ የተለያዩ ፖሊሲዎችንና ስትራቴጂዎችን በመተግበር ላይ ይገኛል።

የኮቪድ-19 ወረርሽኝ ለመከላከልና ለመቆጣጠር ተሻሽሎ የወጣው መመሪያ ቁጥር 882/2014

Dr. Lia Tadesse

 የጤና ሚኒስትር ዶ/ር ሊያ ታደሰ የኮቪድ-19 ወረርሽኝ ለመከላከልና ለመቆጣጠር ተሻሽሎ የወጣው መመሪያ ቁጥር 882/2014 በተመለከተ ጋዜጣዊ መግለጫ ሰተዋል፡፡


ባለፉት ሁለት አመታት በሃገራችን ኢትዮጵያ ወረርሽኙን ለመቆጣጠር እና ለመግታት የተለያዩ መመሪያዎችንና ደንቦችን በማውጣት ተግባራዊ ሲደረግ ቆይቷል፡፡ 

የጤና ሚኒስቴር፣ የክልል የጤና ቢሮዎች እና የተጠሪ ተቋማት ከፍተኛ አመራሮች የጋራ መድረክ ተጀምሯል

JSC

በጋራ የውይይት መድረኩ መክፈቻ ንግግር ያደረጉት የጤና ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴኤታ ዶ/ር ደረጀ ዱጉማ እንደተናገሩት የጤናው ዘርፍ ከፍተኛ አመራሮች የጋራ መድረኩ በዘርፉ የተከናወኑ ዋና ዋና ተግባራት አፈጻጸምን፣ ተግዳሮቶችን እና የተገኙ ልምዶችን በጋራ ለመገምገምና የቀጣይ  አቅጣጫ ላይ ለመግባባት ይረዳል፡፡ 


የተለያየ ግጭት ያለባቸውን ሁሉንም አካባቢዎች በአግባቡ በመዳሰስ እና ሁሉም የኅብረተሰብ ክፍል አስፈላጊውን ድጋፍ እንዲያገኙ፣ በሆስፒታሎች እና በጤና ተቋማት አስፈላጊ ግብዓቶችን በማሟላት የተቋረጡ የሕክምና አገልግሎቶች መልሰው እንዲጀምሩ ማድረግ እንደሚገባ የገለፁት ዶ/ር ደረጀ ዱጉማ ይህም በጋራ የውይይት መድረኩ በትኩረት የሚገመገም አጀንዳ አንዱ መሆኑን አስረድተዋል፡፡

በአማራ እና አፋር ክልሎች ጉዳት ለደረሰባቸው የሆስፒታል ላብራቶሪዎችን መልሶ ለማቋቋም የህክምና ቁሳቁስ ድጋፍ ተደረገ 

donation

6.5 ሚሊዮን ብር የሚያወጣ የላብራቶሪ ህክምና ቁሳቁስ ድጋፍን ያደረገው የኦሃዮ ስቴት ግሎባል ዋን ሄልዝ ሲሆን በጦርነት ጉዳት የደረሰባቸው የህክምና ተቋማትን መልሶ ለማቋቋም የሚውል መሆኑ ተገልጿል፡፡ 


የጤናው ዘርፍ በጦርነቱ ከፍተኛ ውድመት ያሰተናገደ ዘርፍ መሆኑን የገለጹት የጤና ሚኒስቴር ሚንስትር ዴዔታ ዶ/ር አየለ ተሸመ፤ የተደረገው ድጋፍ ያጋጠሙትን ችግሮች ለመቅረፍ የሚረዳ መሆኑን ገልጸዋል፡፡ 


የላብራቶሪ ህክምና ቁሳቁስ ድጋፍ የተደረገላቸው ተቋማት የተሟላ የህክምና አገልግሎት ለመስጠት እንዲችሉ እየተደረገ ያለውን ጥረት የሚደገፍ መሆኑን በመግለጽ ስለተደረገው ድጋፍ በጤና ሚኒስቴር፣ ድጋፍ በተደረገላቸው ተቋማት እና በተቋማቱ አገልግሎት በሚያገኙ ማህበረሰቦች ስም ምስጋና አቅርበዋል፡፡