መድሃኒት የተላመደ የቲቢ በሽታ ከተስፋፋባቸው 33 ሀገራት ዝርዝር ውስጥ ኢትዮጵያ መውጣቷ መልካም አጋጣሚ ነዉ።

Dr. Lia Tadesse

ኢትዮጵያ ዓለም አቀፍ መድሃኒት የተላመደ የቲቢ በሽታን መግታት የድርጊት መርሃ ግብር ተቀብላ እየሰራች ነዉ ያሉት የጤና ሚኒስቴር ሚንስትር ዶ/ር ሊያ ታደሰ ናቸው፡፡ ክብርት ሚኒስትሯ ይህንን ያሉት በምስራቅ መካከለኛና ደቡብ አፍሪቃ (ECSA) ዓመታዊ የቲቢ በሽታ ምርመራ ላብራቶር የማጠናከሪያ ውይይት መድረክ ላይ ነዉ። በአገራችን በቲቢ መከላከል ዙሪያ የተሰሩ ስራዎች አበረታች ለውጥ እያሳዩ መሆኑን የገለጹት ሚኒስትሯ በዋቢነትም በዓለም መድሃኒት የተላመደ የቲቢ በሽታ ከተስፋፋባቸው 33 ሀገራት ዝርዝር ውስጥ ኢትዮጵያ መውጣቷ መልካም አጋጣሚ እንደሆነ ገልጸዋል።


የECSA ዳይሬክተር ጀኔራል ፕ/ር ዮስዋ ደምብስያ እንደተናገሩት የአፍሪካ ችግሮች ለአፍሪካኖች እንዲፈቱ አስታውሰው በግሎባል ፈንድ የቲቢ ላብራቶር ምርመራ ማጠናከሪያ ኘሮጀክት ላለፉት ሰባት ዓመታት ሲያግዙ ለቆዩ ባለድርሻ አካላት ምስጋና አቅርበው ለወደፊትም ይህ ሥራ ተጠናክሮ እንዲቀጥል ድጋፋቸው እንደሚያስፈልግ ጠቁመዋል፡፡

ጳጉሜ 1 የበጎ ፈቃደኝነት ቀን አስመልክቶ የጤና ሚኒስቴር፣  የትምህርት ሚኒስቴር እና የስራና ክህሎት ሚኒስቴር በጋራ የሚያዘግጁት የሙሉ ቀን መርሃ ግብር በሚኒሊክ አጠቃላይ ሁለተኛ ደረጃ እና የመጀመርያ ደረጃ ትምህርት ቤት በተለያዩ ዝግጅቶች ተጀምሯል።

Dr. Lia Tadesse

ዛሬ ጳጉሜ 1 የበጎ ፈቃደኝነት ቀን በማስመልከት በአራዳ ክፍለ ከተማ በሚኒሊክ አጠቃላይ ሁለተኛ ደረጃ እና የመጀመርያ ደረጃ ትምህርት ቤት የትምህርት ተቋማትን ፅዱና ውብ በማድረግ እንደዚሁም የተተከሉ ችግኞችን በማረም ፣ በመኮትኮት እና በመንከባከብ መርሃ ግብር  ተጀምሯል።

በማስጀመሪያ መርሀ ግብሩ ላይ የጤና ሚኒስትር ዶ/ር ሊያ ታደሰ፣ የትምህርት ሚኒስትር ፕሮፌስር ብርሃኑ ነጋ እና ሌሎች ጥሪ የተደረገላቸዉ እንግዶች ተገኝተዋል፡፡

መርሀ ግብሩ ለ2015 ዓ.ም የትምህርት ዘመን የትምህርት ተቋማት ለተማሪዎች ምቹ ፣ ፅዱ፣ ውብና ማራኪ እንዲሁም ሳቢ እንዲሆኑ እና ለመማር ማስተማሩ ሂደት ጉልህ ሚና እንዲኖራቸው ለማድረግ የሚያስችል ነው።

ጳጉሜ 1 የበጎ ፈቃደኝነት ቀን በተለያዩ መርሀ ግብሮች የሚቀጥል ይሆናል።

"ድህረ ጦርነትና የአጥንት ህክምና" በሚል መሪ ቃል 16ኛ የኢትዮጵያ የአጥንት ህክምና ሃኪሞች ማህበር አመታዊ ጉባኤ በአዲስ አበባ ተካሄደ

Dr. Ayele Teshome

በጉባዔው ላይ በክብር እንግድነት ተገኝተው ንግግር ያደረጉት የጤና ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴኤታ ዶ/ር አየለ ተሾመ የማህበሩ አባላት በግለሰብም ደረጃም ሆነ እንደ ተቋም ሃገር በተቸገረችበት ጊዜ ሁሉ በሰው ሰራሽና ተፈጥሮአዊ አደጋዎች በተለይም በጦርነት ጉዳት ለሚደርስባቸው የኢትዮጵያ ጀግና ሰራዊት አባላትን ህይወት ለመታደግ ላበረከቱት እና እያበረከቱት ያለው አገልግሎት በታሪክ መዝገብ ላይ መፃፉን ጠቅሰው ለአበርክቶዓቸው ሁሉ ኢትዮጵያ ታመሰግናለች ብለዋል።

እኤአ በ2030 የቲቢ በሽታን ለመግታት ቀጣይነት ባለዉ የልማት ግብ የተያዘዉ ዕቅድን ለማሳካት ተገቢዉን ትኩረት ሳያገኝ የቆየዉ የህጻናትና አፍላ ወጣቶች የቲቢ በሽታ ልይታ፣ ምርመራና ህክምና ላይ ትኩረት በማድረግ መስራት  ያስፈልጋል።

Dr. Lia Tadesse

የኢፌድሪ ጤና ሚኒስትር ክብርት ዶ/ር ሊያ ታደሰ በሎሜ ቶጎ እየተካሄደ ባለዉ 72 ኛው የአፍርካ አህጉር የአለም ጤና ድርጅት መድረክ ላይ እንደገለጹት በኢትዮጵያ በ2015 የጸደቀዉ የህጻናትና አፍላ ወጣቶች የቲቢ በሽታ ፍኖተ ካርታ ተግባራዊ መሆን ከጀመረ ወዲህ ህጻናትና አፍላ ወጣቶችን ከቲቢ በሽታ የመከላከልና ህክምና ስራ መሻሻሉን ተናግረዋል።  


በኢትዮጵያ በተሰራዉ ስራ በበሽታዉ የሚያዙና የሚሞቱ ሰዎች ቁጥር  ቢቀንስም የቲቢ በሸታ እንዲሁም የቲቢ -ኤች አይቪ ጫና አሁንም ከፍተኛ በሆነባቸዉ 30 አገሮች አንዷ መሆኗን ያወሱት ዶ/ር ሊያ፣ የቲቢ በሽታን ለመከላከልና ለመቆጣጠር የሚሰሩ ስራዎች ለቲቢ ይበልጥ ተጋላጭ የሆኑና የተዘነጉ የህብረተሰብ ክፍሎች ላይ ትኩረት ማድረግ ይገባል ብለዋል።

“በጎነት ለጤናችን’’በሚል ነፃ የጤና ምርመራ እና የህክምና የበጎ ፍቃድ አገልግሎት በክልሎችና በከተማ መስተዳደሮች ተጠናክሮ ቀጥሏል፡፡

voluntary service

በአገር አቀፍ ደረጃ በአንድ ሳምንት ከመቶ ሺ በላይ ለሚሆኑ ዜጎች የነጻ የጤና ምርመራ እና ህክምና አገልግለት ለመስጠት የተጀመረው  ሰው- ተኮር የበጎ ፈቃድ የተግባር ዘመቻ  በሁሉም ክልሎችና በከተማ መስተዳደሮች በተጠናከረ መልኩ ቀጥሏል፡፡


በዘመቻውም የጤና አጠባበቅ ትምህርትና ምክር አገልግሎት ፣ በተላላፊና ተላላፊ ያልሆኑ በሽታዎች ፣የኮሌራና ሌሎች ውሀ ወለድ በሽታዎች፣ ወባ፣ ኤች አይ ቪ ፣ ቲቪ ፣ ኮቪድ-19፣ የካንሰር ህመምና ሌሎች ትኩረት በሚሹ የጤና ጉዳዮች ላይ ማለትም የደም ግፊት ፣የደም የስኳር መጠን፣ ከአንገት በላይ፣ የአይን፣ የቆዳ፣የስነ ምግብ፣ የአእምሮ ጤና  እና ሌሎች የጤና አገልግሎቶች እየተሰጡ ይገኛሉ፡፡

የኢትዮጵያ ልዑካን ቡድን በ72 ኛው የአፍርካ አህጉር የአለም ጤና ድርጅት መድረክ ላይ እየተሳተፈ ነው።

Dr. Dereje Duguma

ዛሬ በሎሜ ቶጎ የተጀመረዉ 72 ኛው የአፍርካ አህጉር የአለም ጤና ድርጅት መድረክ ላይ የኢትዮጵያ ልዑካን ቡድን እየተሳተፈ ይገኛል።  

                         
ይህ 72 ኛው የአፍሪከ አህጉር ከዓለም ጤና ድርጅት ስድስት የአህጉራዊ አስተዳደር አካላት አንዱ ሲሆን 47 አባል ሀገራት ያሉት  የአፍሪካ ክልል ሀገራት የሚወክሉበት  ኮሚቴ ነው፡፡ 


በመድረኩም የአፍርካ የአለም ጤና ንኡስ ኮሚቴዎች እባላት የሚሰየም ሲሆን እኤአ የ2022 የስራ እፈጻጸም እንዲሁም የአፍሪካ ማህበረሰብ ጤና አሁናዊና ቀጣይ  ስትራቴጅክ ጉዳዮች ከአለማችን ማህበረሰብ ጤና ጋር ያለዉ አጠቃላይ ሁኔታ በመድረኩ ቀርበው ምክክርና ውይይት የሚደረግ ይሆናል። 


መድረኩም ለቀጠይ 5 ቀናት በሎሜ ቶጎ የሚቀጥል ይሆናል።

የኤች.አይ.ቪ/ኤድስ መከላከል እና መቆጣጠር የ2015 እቅድ ማስተዋወቂያ እና የምክክር መድረክ ተካሄደ

Hiwot Solomon

የዘንድሮው አመታዊ አገራዊ የኤች.አይ.ቪ/ኤድስ መከላከል እና መቆጣጠር እቅድ የክልል እና ከተማ መስተዳድር ጤና ቢሮዎችን እና ኤች.አይ.ቪ/ኤድስ መከላከል እና መቆጣጠር ጽህፈት ቤቶችን ሴክተር መስሪያ ቤቶችን እንዲሁም ሌሎች ባለድርሻ አካላትን በማስተባበር የተዘጋጀ ሲሆን፤ የ2014 በጀት አመት አፈጻጸምን በመገምገም 2015 በጀት አመት እቅድ ዝግጅት የጋራ ለማድረግና ቀጣይ እርምጃዎችን ለማፋጠን ይረዳ ዘንድ የተዘጋጀ የምክክር መድረክ መሆኑን በጤና ሚኒስቴር የበሽታዎች መከላከልና መቆጣጠር ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር ወ/ሮ ህይወት ሰለሞን ገልጸዋል፡፡

በተለያዩ አካላት ሲመራ የነበረው የኤች.አይ.ቪ/ኤድስ መከላከል እና መቆጣጠር ስራ አዲስ በተቀመጠው አቅጣጫ መሰረት በአንድ እንዲመራ መደረጉ መልካም ነው ያሉት ዳይሬክተሯ፤ በአለም አቀፍ ደረጃ የተቀመጠውን አቅጣጫ በማሳካት የኤች.አይ.ቪ/ኤድስ ስርጭትን በ2030 ለማስቆም መስራት ይገባል ብለዋል፡፡

የኮቪድ 19 ወረርሽኝን በመከላከልና በመቆጣጠር ረገድ ሚና ለነበራቸው የቅዱስ ጳውሎስ ሆስፒታል ሚሊኒየም ሕክምና ኮሌጅ ባለሙያዎች የምስጋና መርሀግብር ተካሄደ።

St Paul

በቅዱስ ጳውሎስ ሆስፒታል ሚሊኒየም ሕክምና ኮሌጅ በተዘጋጀዉ ፕሮግራም ላይ የተገኙት የጤና ሚኒስቴር ሚኒስትር ዶ/ር ሊያ ታደሰ ባደረጉት ንግግር በሀገራችን ባለፉት ጊዜያት በተከሰቱ የኮቪድ 19 ወረርሽኝ እና ጦርነት በቀዳሚነት ምላሽ በመስጠት ላበረከቱት አስተዋጽዖ አመስግነዋል። የቅዱስ ጳውሎስ ሆስፒታል ሚሊኒየም ኮሌጅ አመራሮች እና ሰራተኞች በዛ አስቸጋሪ ወቅት ዋጋ ከፍለው ላሳዩት ርብርብ ሚኒስቴር መስሪያቤቱ እውቅና እና ምስጋና ያቀርባል ብለዋል።


በዚያ ወረርሽኝ ወቅት የሆስፒታሉ አመራሮች እና ሰራተኞች ቅድሚያ ተነሳሽነት በማሳደር በሚሊኒየም የኮቪድ ማእከል መስዋትነት በመክፈል ጭምር ለሰሩት ስራ እና በሌሎች ክልሎችም ማእከላቱ እንዲስፋፉ በማገዝ ላበረከታችሁት አስተዋጽዎ ምስጋና ይገባችዃል ያሉት ዶክተር ሊያ ትልቅ ስራ እና ሀላፊነትም መወጣት የሚችል አቅም እንዳለን የተገነዘብንበትና የኮራንበት ስራም ነው ብለዋል።

የኢትዮጵያ የውስጥ ደዌ ህክምና ማህበር 7ኛው ዓመታዊ ሳይንሳዊ ጉባኤ ተካሄደ

group picture

በእለቱ በክብር እንግድነት የተገኙት የጤና ሚኒስትር ዴኤታ ዶክተር አየለ ተሾመ በጉባኤው መክፈቻ ላይ ባደረጉት ንግግር እንደገለጹት ባለፉት ሁለት አስርት አመታት የኢትዮጵያ ጤና ፖሊሲ በማህበረሰብ ጤና ማጎልበት፣ በሽታ መከላከልና የጤና አገልግሎት ሽፋን ማሻሻል ላይ ትኩረት አደርጎ የተሰራበት እና በዚህም ብዙ ስኬቶች  የተመዘገቡበት እንደነበር የተናገሩ ሲሆን በአሁኑ ወቅት ግን የተላላፊ በሽታዎች ብቻ ሳይሆኑ ተላላፊ ያልሆኑ በሽታዎች እና አደጋዎችም በከፍተኛ ሁኔታ መጨመራቸውን ተከትሎ የከፍተኛ የፈውስ ህክምና ፍላጎትም እንዲሁ የጨመረበት ወቅት በመሆኑ የጤና ሚኒስቴር ለዚሁ ምላሽ በሁሉም የአገሪቱ ክፍሎች የሶስተኛ ደረጃ /tertiary care/  አገልግሎት ተደራሽነትንና ጥራትን ለማሻሻል እየሰራ እንደሚገኝ ተናግረዋል፡፡ 

አባቶች፣ የቤተሰብ አባላትና ማህበረሰቡ ለሚያጠቡ እናቶች ትኩረት ሊሰጡ ይገባል

group picture

"ምቹ ሁኔታ ለሚያጠቡ እናቶች፣ እናስተምር፣ እንደግፍ!!" በሚል መሪ ቃል በአለም ለ30ኛ ጊዜ በሃገራችን ደግሞ ለ14ኛ ጊዜ የጡት ማጥባት ሳምንት እየተከበረ ሲሆን ዛሬ በደብረብርሃን ወይንሸት የተፈናቃዮች መጠለያ ከሚገኙ እናቶችና ህጻናት ጋር በአሉ ተከብሯል። 


በጤና ሚኒስቴር ሃገር አቀፍ የስርዓተ ምግብ ፕሮግራም አስተባባሪ የሆኑት ወ/ሮ ህይወት ዳርሰኔ በስነስርዓቱ ላይ እንደ ተናገሩት እናቶች ልጆቻቸውን እስከ ስድስት ወራት ጡት ብቻ ማጥባታቸው የህጻኑን ጤንነት ከመጠበቅና የተስተካከለ እድገት እንዲኖረው ከማስቻሉ ባለፈ ሃገራዊ ጥቅሙ ከፍተኛ ነው ብለዋል። እናቶች በማይመች ሁኔታ ውስጥም ቢሆኑ ለልጆቻቸው የጡት ወተትን መስጠት ማቋረጥ እንደሌለባቸው ለእናቶቹ አስገንዝበው አባቶች፣ የቤተሰብ አባላትና ማህበረሰቡም ለሚያጠቡ እናቶች ትኩረት ሊሰጡ እንደሚገባ አስገንዝበዋል።