Articles

የእናት ጡት ወተት የህይወት ምግብ!

Dr. MESSERET ZELALEM

“ምቹ ሁኔታ ለሚያጠቡ እናቶች፤ እናስተምር፤ እንደግፍ!!” በሚል መሪ ቃል የዘንድሮው የጡት ማጥባት ሣምንት በዓለም ለሰላሳኛ በሀገራችን ደግሞ ለአስራ አራተኛ ጊዜ እየተከበረ ነው፡፡

የሥርዓተ ምግብ ችግሮች በዓለም ላይ በየዓመቱ ወደ አምስት ሚሊዮን ሕፃናት ህመምና ሞት ምክንያት ነው ያሉት የጤና ሚኒስቴር የእናቶች ህፃናት እና የስርዓት ምግብ ዳይሬክተር ዶ/ር መሰረት ዘላለም ከፅንስ ጀምሮ እስከ ሁለት ዓመት ዕድሜ ባለው ጊዜ ማስተካከል ካልተቻለ መቀንጨር እና ሌሎች የምግብ አለመመጣጠን ችግሮች ሊከሰት እና በቀጣዩ የእድሜ ክልል ከትውልድ ወደ ትውልድ ሊተላለፍ የሚችል አመጋገብ ችግር ይሆናል ብለዋል።

ኦሀዮ ስቴት ዩኒቨርሲቲ ግሎባል ዋን ሄልዝ ፕሮግራም  በሰሜኑ ክፍል በነበረው ጦረነት ለተጎዱ የጤና ተቋማት ድጋፍ አደረገ

Ohio State University

በዛሬው እለት የተደረገው ድጋፍ 9 ሚሊዮን ብር የሚያወጡ የላብራቶሪ እቃዎች መሆናቸው ማወቅ የተቻለ ሲሆኑ ድጋፉ የተደረገው በአማራ እና በአፋር በክልል ለሚገኙ ስድስት ሆስፒታሎች ሲሆን በስድስቱ ሆስፒታሎች ውስጥ ላሉ የላብራቶሪ ክፍሎችን መልሶ ለማደረጃት የሚረዳ ድጋፍ ነው፡፡


በርክክብ ስነስርዓቱ ላይ ንግግር ያደረጉት የጤና ሚኒስትር ዶክተር ሊያ ታደሰ እንዳሉት በአገራቱ የነበረው ጦርነት የጤና ተቋማትን ማውደሙን ተከትሎ መልሶ ለማቋቋም በተደረገው ርብርብ ሁሉም ሆስፒታሎች ወደ ስራ እንዲገቡ መደረጉን አንስተዋል፡፡ ኦሀዮ ስቴት ዩኒቨርሲቲ ግሎባል ዋን  ሄልዝ ፕሮግራም ለዚህ ችግር ትኩረት በመስጠት  የሆስፒታሎችን ላብራቶሪዎች ሙሉ ለሙሉ ለመደገፍ መቻሉን ዶክተር ሊያ የተናገሩ ሲሆን በቴክኒክም የማጠናከር ስራ እየሰራ መሆኑንም ነው የገለጹት፡፡ 

የግሎባል ፈንድ አፈጻጸም እና ትግበራ በተመለከተ ከሲውዘርላንድ ከመጡ ከፍተኛ የተቋሙ አባላት ጋር ውይይት ተደረገ

Global Fund

ሲውዘርላንድ ጄኔቭ ከሚገኘዉ የግሎባል ፈንድ ዋና መስሪያቤት የመጣው ከፍተኛ የአመራርና የባለሙያዎች ቡድን ጋር በደተረገው ውይይት ላይ የሃይ ኢምፓክት አፍሪካ ሄድ ኦፍ ዲፓርትመንት እና የዴሊጌሽኑ መሪ የሆኑት ሊንደን ሞሪሰን እንዳሉት ኢትዮጵያ የተላያዩ ችግሮች ያጋጠሟት ቢሆንም በግሎባል ፈንድ ድጋፍ የሚደረግላቸዉ የጤና ፕሮግራሞች አፈጻጸም ግን ጥሩ በመሆኑ ደስተኞች መሆናቸውን ተናግረዋል፡፡


በግሎባል ፈንድ ስር የሚከወኑ ፕሮግራሞችን እና የኮቪድ መከላከል ስራዎች መልካም ውጤት ያስገኙ መሆናቸው የገለጹት የጤና ሚኒስቴር ዶ/ር ሊያ ታደሰ ናቸው፡፡ የውጭ ምንዛሬ አለመረጋጋት እና ግጭት የግሎባል ፈንድ አፈጻፀም እና ትግበራ ላይ ያጋጠሙ ችግሮች እንደሆኑ ዶ/ር ሊያ ተናግረዋል፡፡ ያጋጠሙ የአቅርቦት ችግሮችን መቅረፍ ይገባል ያሉት ዶ/ር ሊያ፣ በግሎባል ፈንድ አፈጻጸም እና ትግበራ ላይ አጋር ድርጅቶች ያደረጉትን ተሳትፎ አድንቀዋል፡፡