የጤና ኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ዳይሬክቶሬት
የጤና ኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ የስራ ሂደት የጤናዉን ዘርፍ የአገልግሎት አሰጣጥ ጥራትን፤ ተደራሽነትን እና ፍትሐዊነትን ለማሻሻል፤ አገር በቀልና አዳዲስ ፈጠራ የታከለበት(innovative) በሆኑ ቴክኖሎጂዎች እየታገዘ የጤና አገልግሎትን መተግበር፤ መረጃን በወቅቱ፣በጥራት ለመሰብሰብ፣ ለመጠቀም እና ለማስተላለፍ የሚያስችል የጤና ኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ በጤናው ዘርፍ ተግባራዊ ለማድረግ እየሰራ ይገኛል፡፡
የሥራ ሂደቱ እንደ አጠቃላይ ከሚተግብራቸዉ ግቦች መካከል ዋናዎቹ እንደ ወጪ ቆጣቢ፣ አገር በቀል እና በፈጠራ ላይ የተመሰረቱ የኢንፎርሜሽን እና ኮሙኒኬሽን ቴክኖሎጂዎችን በመቀመር ከአገር ነባራዊ ሁኔታ ጋር በማዛመድ የጤና አገልግሎት ተደራሽነት፣ ጥራት እና ፍትሃዊነትን ወደ ላቀ ሁኔታ ማሻገር ነዉ፡፡