የእናቶች ጤና

Maternal Health

በኢትዮጵያ የእናቶች ጤና አጠቃላይ እይታ

ኢትዮጵያ ባለፉት አስርት ዓመታት በእናቶች ሞት ላይ አስገራሚ ለውጥ አድርጋለች፣ MMR በ 2000ዓ.ም 871 ከ100,000 የነበረ ሲሆን በ2017ዓ.ም  ወደ 401 ከ100,000 ቀንሷል፤  ይህ በየዓመቱ ወደ 12,000 የእናቶች ሞት ነው። ቀጥተኛ የወሊድ ችግሮች 85% የሚሆኑት የሞት መንስኤዎች ናቸው። የረጅም ጊዜ ሁኔታዎች ሴቶች ላይ ከወሊድ ጋር የተዛመዱ በሽታዎችን አስከትለዋል። ለምሳሌ ፊስቱላ ፣ የማሕፀን ተፈጥሯዊ ቦታ መዛባት፣ ሥር የሰደደ የወገብ አጥንት ህመም ፣ ድብርት እና ድካም። በተለይ በኢትዮጵያ ውስጥ ፊስቱላ የተለመደ ሲሆን በዋነኝነት በልጃገርረድ ዕድሜ ከሚፈጠር እርግዝና እና ችላ ከተባለ ረዥም ምጥ ጋር ተዳምሮ የሚፈጥረው ነው። ከፍተኛ የእናቶች ሞት መጠን በቀጥታ ከ ከፍተኛ የአራስ ሕፃናትሞት መጠን (29/1,000 በህይወት የተወለዱ ህጻናት )ጋር ይያያዛል። ይህ በወሊድ ጊዜ እናቶቹ የነበሩበትን አስቸጋሪ ሁኔታ ያንፀባርቃል። ለአራስ ሕፃናት ሞት ዋነኛ መንስኤ

ብሔራዊ የአመጋገብ ፕሮግራም

nutrition

መግቢያ

በኢትዮጵያ ውስጥ ባለፉት አስርት ዓመታት የምግብ እጥረትን በመቀነስ አበረታች እድገት ተመዝግቧል። ሆኖም ነባር የምግብ እጥረት ደረጃ በጣም ከፍተኛ ከመሆኑ የተነሳ ኢትዮጵያ አሁንም በአመጋገብ ላይ ከፍተኛ ኢንቨስትመንቷን መቀጠል አለባት።

 

የተስፋፋ የክትባት መርሃ ግብር (EPI)

epi

የክትባት ፕሮግራም ወጪ ቆጣቢ ከሆኑ የጤና ጣልቃ ገብነቶች አንዱ ሲሆን አናሳ የህክምና ተደራሽነት ያላቸውና ተጋላጭ የሆኑ ሰዎችን በተረጋገጡ ስልቶች ያግዛል። በክትባት ሊከላከሏቸው የሚቻሉ በሽታዎች(VPD) ጋር የተዛመዱ ሕመሞችን እና ሞቶችን ከመቀነስ አኳያ የሚለኩ ስኬቶች ብሔራዊ የክትባት መርሃ ግብር በኢትዮጵያ በ1980G.C ከተጀመረ ጀምሮ ተመዝግበዋል። አዳዲስ እና በተገቢው መጠን ያላገለገሉ ክትባቶችን ደረጃ በደረጃ በማስተዋወቅ በክትባት ሊከላከሏቸው የሚቻሉ በሽታዎችን በመቀነስ አስደናቂ ስኬቶች ተገኝተዋል፤ እናም በአሁኑ የክትባት መርሃ ግብር ውስጥ የተካተቱ አጠቃላይ አንቲጂኖች ወደ አስራ ሁለት ደርሰዋል። አገሪቱ በክትባት እና የክትባት ሂደት ጉዳይ ላይ መርሃ ግብሩን የሚመራ ገለልተኛ የባለሙያ አካል የሆነውን ብሔራዊ የክትባት ቴክኒካዊ አማካሪ ቡድን (NITAG) አቋቁማለች። የ ቅንጅት ማስተባበሪያ ኮሚቴ (ICC) ለረጅም ጊዜ የቆየ ሲሆን በEPI ላይ የአጋር ትብብርን ለመደገፍ የቻሉ ቅንጅቶችን እና ዋና ውሳኔዎችን የማከናወን

የሪፎርምና መልካም አስተዳደር ዳይሬክቶሬት

ራዕይ

  • ጤናማ አምራችና የበለፀገ ማህበረሰብ ተፈጥሮ ማየት ነው፡፡

ተልዕኮ

  • ውጤታማ በሆነ መንገድ የጤና ሪፎርሞችንና የመልካም አስተዳደር መርሆዎችን በመተግበር፤ የተናበበና ተገልጋይ ተኮር ለውጥ አምጪ ተግባራትን በሀገር አቀፍ ደረጃ  በመፈጸም  የጤና የአገልግሎት አሰጣጥን ማሻሻል፡፡

አላማ

  1. የለውጥ አምጪና የእርስ በዕርስ የስራ ግንኙነት ተግባራት ውጤታማ በማድረግ የስራ አፈጻጸምን ማሻሻል  
  2. የዜጎች ቻርተርን ትግበራን በማጠናከር የዘርፉን የስታንዳርድ ትግበራ አቅምን ለማሻሻል 
  3. የአገልግሎት ማሻሻያ ጥምረትን በመተግበር የፕሮግራሞችን አፈጻጸም ማሻሻል 
  4. የመልካም አስተዳደር መርሆዎችን፣ የማህበረሰብ አስተያየት ምዘና ስርዓትን፣ እንዲሁም የአመራር ተጠያቂነት ስርዓትን በመተግበር የዘርፉን ሀ

ለፖሊሲ ዕቅድ፣ ክትትልና ግምገማ ዳይሬክቶሬት

ራዕይ

በማስረጃ ላይ በተመሰረተ ዕቅድ እና ውሳኔ አሰጣጥ አማካኝነት የሕዝቡን የተሻሻለ የጤና ሁኔታ ለማየት

ተልዕኮ

በጤናው ዘርፍ ተግባራዊ የሆነ አንድ ዕቅድ ፣ አንድ ሪፖርትና አንድ በጀት መርሆዎችን ተቋማዊ በማድረግ በማስረጃ ላይ የተመሠረተ ዕቅድንና ውሳኔ አሰጣጥን ማሳደግ። እነዚህ በዋነኝነት የሚፈፀሙት ጥራት ያለውን መረጃ ተደራሽነትንና አጠቃቀምን በማሻሻል ፣ በሁሉም ደረጃ የመረጃ አስተዳደር አቅምን በማሻሻል ፣ የክትትል እና የግምገማ አሰራሮችን በማሻሻል ፣ መደበኛ የመረጃ ማሰባሰብ እና የሪፖርት ስልቶችን ስታንዳርዳይዝ በማድረግ፣ ጥናቶችን እና ግምገማዎችን በማካሄድ ነው።

ዳራ

ለፖሊሲ ዕቅድ ፣ ክትትልና ግምገማ ዳይሬክቶሬቱ በሚኒስቴር ደረጃ ከሚገኙ ዋና የሥራ ሂደቶች አንዱ ሲሆን የፖሊሲ ፣ የዕቅድ ፣ የክትትልና የግምገማ ሥራዎችን የማስተዳደር ዋና ኃላፊነት ያለበት ነው።

ለመድኃኒትና የሕክምና መሣሪያዎች አስተዳደር ዳይሬክቶሬት

ራዕይ

ጤናማ ፣ አምራችና የበለፀገ ማህበረሰብን መፍጠር

ተልዕኮ


ጠንካራ የመድሃኒት ቤት አገልግሎትን ማቋቋም ፣ የፀረ ተሕዋስያን መድሃኒት መቋቋምን (AMR) መከላከል እና መቆጣጠር፣ የሀብት ብክነትን የሚቀንስና በአገሪቱ ውስጥ ደህንነቱና ጥራቱ የተጠበቀ ተመጣጣኝ ዋጋ ያለው የህክምና ግብዓቶች አቅርቦትን የሚያረጋግጥ ጠንካራ የአቅርቦት ሰንሰለትና የጤና አገልግሎት ቴክኖሎጂ አስተዳደር ስርዓትን ማቋቋም፣ መደገፍና ማስተዳደር።

ዓላማ

በዘመናዊና የተረጋገጡ የአሠራር ዘዴዎች እና ስርዓቶች በመደገፍ በጤና ተቋማት ውስጥ ውጤታማ የመድኃኒት ቤት አገልግሎትን እውን ማድረግ

ዘመናዊ የአስተዳደር ሥርዓትን ተጠቅሞ የመድኃኒት አቅርቦት ሰንሰለት ሂደት ከግዥ ዕቅድ እስከ አፈፃፀም ድረስ በማመቻቸት የጤና ተቋማት ትክክለኛና ጥራት ያላቸውን የመድኃኒት ምርቶች እንዲኖራቸው ማድረግ

ህግ ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት

ራዕይ

በ 2015 E.C ሚኒስቴሩ ከማንኛውም የፍርድ ቤት ጉዳዮች ነፃ ሆኖ ማየት

ተልዕኮ

የእኛ ተልእኮ ለሚኒስቴሩ የሕግ ውክልናን፣ ጥራት ያለው አገልግሎትን እና የሚኒስቴሩን ተልዕኮ ለማሳካት የሚረዳ ሁሉን አቀፍ የሕግ አገልግሎት መስጠት ነው።

የዳይሬክቶሬቱ ዋና ሚናዎች እና ኃላፊነቶች፡

  1. በማንኛውም የሕግ ጉዳዮች ላይ የሕግ ምክሮችን እና አስተያየቶችን መስጠት ፣
  2. የሲቪል እና የወንጀል ጉዳዮችን (የፍርድ ቤት እና የፖሊስ ጣቢያዎችን) መከታተል ፤
  3. የሕግ ሰነዶችን (አዋጅ ፣ ደንብ ፣ መመሪያ ፣ ስምምነት እና የመግባቢያ ማስታወሻዎችን)ማርቀቅ;
  4. በተለያዩ ሕጎች ላይ ግንዛቤ መፍጠር 
  5. ከሚኒስቴሩ አጠቃላይ የሕግ ጉዳዮች ጋር የተያያዙ ሥራዎችን ማከናወን
     

የጤና እና ጤና ነክ ተቋማት ቁጥጥር ዳይሬክቶሬት

መግቢያ

የጤና እና ጤና ነክ ተቋማት ቁጥጥር ዳይሬክቶሬት በፌደራል መንግስት ስር የሚገኙ የጤና እና ጤና ነክ ተቋማትን ለመቆጣጠርና የክልሉን ጤና ተቆጣጣሪ አካላት ለመደገፍ የተቋቋመ ዳይሬክቶሬት ነው። ዳይሬክቶሬቱ ሁለት የጉዳይ ቡድኖች አሉት ፤ እነዚህም የጤና ተቋማት ተቆጣጣሪ ጉዳይ ቡድንና የጤና ነክ ተቋማት ተቆጣጣሪ የጉዳይ ቡድን ናቸው።

ራዕይ

ደህንነቱ የተጠበቀና ጥራት ያለው የጤና እና ጤና ነክ አገልግሎቶችን ለህብረተሰቡ ማድረስ