የቦሩ ሜዳ ጠቅላላ ሆስፒታል በጦርነት ከደረሰበት ጉዳት አገግሞ ሁሉንም አገልግሎቶች በመስጠት ላይ ነው::
የጤና ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴኤታ ዶ/ር አየለ ተሾመ የሆስፒታሉን የተለያዩ የስራ ክፍሎች ተዘዋውረው በጎበኙበት ወቅት እንደገለፁት ሆስፒታሉ ከደረሱበት ችግሮች ፈጥኖ በማገገም ለተገልጋዮች የተሟላ አገልግሎት መስጠት መጀመሩ የሚደነቅ ነው ብለዋል።
የቦሩ ሜዳ ጠቅላላ ሆስፒታል በጦርነቱ ወቅት ከፍተኛ ውድመት ከደረሰባቸው ሆስፒታሎች አንዱ እንደነበር ያስታወሱት ዶ/ር አየለ የተሟላ አገልግሎት እንዲሰጥ የተረባረቡትን ሁሉ አመስግነው በቀጣይም የጤና ሚኒስቴር የጎደሉ የህክምና መሳሪያዎችን ለማሟላት እየተፈፀሙ ያሉ ግዢዎችን በማፋጠን ሆስፒታሉ የሚጠናከርባቸውን አማራጮች ሁሉ እንደሚያመቻች ተናግረዋል።