ችላ የተባሉ የትሮፒካል በሽታዎች (NTDs) ፕሮግራም
ችላ የተባሉ የትሮፒካል በሽታዎች (NTDs) በዓለም ዙሪያ ከአንድ ቢሊዮን የሚበልጡ ሰዎች ላይ ከባድ ህመም የሚያስከትሉ የጥገኛ ህዋስና የባክቴሪያ በሽታዎች ስብስብ ናቸው። የኢትዮጵያ ጤና ጥበቃ ሚኒስቴር ለስምንት በሽታዎች የህዝብ ጤና ላይ ባላቸው ተፅእኖ መሰረት ቅድሚያ ሰጥቷል። እነዚህም ዓይን ማዝ(ትራኮማ) ፣ በአፈር የሚተላለፉ ሄልሚንትስ (STH) ፣ ሺስቶማሲያሲስ፣ ሊምፋቲክ ፊላሪያሲስ (LF) ፣ ኦንኮሴርካ(ኦንኮ) ፣ ድራንኩላ/ጊኒዎርም (GWD) ፣ ቁንጭር(ሌሽማንያሲስ) እና ፖዶኮኒኦሲስ ናቸው። የዓለም ጤና ድርጅት(WHO) ስኬቢስን እንደ አንድ NTD በቅርቡ እውቅና ሰቶታል።