የሪፎርምና መልካም አስተዳደር ዳይሬክቶሬት

ራዕይ

  • ጤናማ አምራችና የበለፀገ ማህበረሰብ ተፈጥሮ ማየት ነው፡፡

ተልዕኮ

  • ውጤታማ በሆነ መንገድ የጤና ሪፎርሞችንና የመልካም አስተዳደር መርሆዎችን በመተግበር፤ የተናበበና ተገልጋይ ተኮር ለውጥ አምጪ ተግባራትን በሀገር አቀፍ ደረጃ  በመፈጸም  የጤና የአገልግሎት አሰጣጥን ማሻሻል፡፡

አላማ

  1. የለውጥ አምጪና የእርስ በዕርስ የስራ ግንኙነት ተግባራት ውጤታማ በማድረግ የስራ አፈጻጸምን ማሻሻል  
  2. የዜጎች ቻርተርን ትግበራን በማጠናከር የዘርፉን የስታንዳርድ ትግበራ አቅምን ለማሻሻል 
  3. የአገልግሎት ማሻሻያ ጥምረትን በመተግበር የፕሮግራሞችን አፈጻጸም ማሻሻል 
  4. የመልካም አስተዳደር መርሆዎችን፣ የማህበረሰብ አስተያየት ምዘና ስርዓትን፣ እንዲሁም የአመራር ተጠያቂነት ስርዓትን በመተግበር የዘርፉን ሀብት አጠቃቀምን ከብክነት መከላከልና የተጠያቂነት ስርዓትን ማጎልበት፡፡ 
  5. የተገልጋዮችን ሃሳብና አስተያየት እንዲሁም ቅሬታዎች በተገቢው ምላሽ በመስጠት  አገልግሎቶች አሰጣጥ ጥራት ደረጃን ማሻሻል 
  6. የማህበረሰብ አገልግሎት ማሻሻያ ካውንስል አሰራር ስርዓትን ማጠናከር 


የሪፎርምና መልካም አስተዳደር  ዳይሬክቶሬት ተግባር

  • በጤናው ዘርፍ የሚተገበሩ የሪፎርም ፖሊሲ፣ ስትራቴጂ፣ ፍኖተ ካርታ፣ እንዲሁም ማኑዋሎችን ማዘጋጀትና መተግበር
  • የሆስፒታል መልካም አስተዳደር ኢንዴክስ ልኬት ምዘና ማካሄድና መከታተል 
  • የሆስፒታል መልካም አስተዳደር ኢንዴክስ ልኬት ምዘና ተቋማዊ ማድረግና አፈጻጸሙን መከታተል
  • በመጀመሪያ የጤና አገልግሎት መስጫ ተቋማት ውስጥ የማህበረሰብ አስተያየት ምዘና ስርዓትን ትግበራን ማካሄድ 
  • የጤናው ዘርፍ የለውጥና መልካም አስተዳደር ስራዎች ማሻሻያ ዕቅድ እንዲታቀድ ማድረግና አገልግሎቶች እንዲሻሻሉ ማድረግ 
  •  ውጤታማነታቸው የተረጋገጡና ለውጥ አምጪ ስትራቴጂዎችን ለጤናው ዘርፍ በሚመች መልኩ በመለወጥ መተግበር
  • የጤና ተቋማትን አፈጻጸም የክትትልና ድጋፋ ግምገማ ስርዓቶችን መተግበር 
  • የተገልጋዮችን አስተያየት መቀበል፣ የሚቀርቡ ቅሬታዎችን መመርመርና ተገቢውን ምላሽ መስጠት፡፡
  • የለውጥና መልካም አስተዳደር ፕሮግራሞችና ተግባራትን አቅም ማጎልበቻ ስልጠናዎችን መስጠት 
  • የክልሎች፣ የሚኒስቴር መስሪያ ቤቱንና የተጠሪ ተቋማት የሪፎርም ተሳትፎ  የሚያሳድጉ  ተግባራትን መከወን 
  • የዜጎች ቻርተር ስታንዳርድ ተቋማዊ ማድረግ 
  • የአገልግሎት ማሻሻያ ካውንስል ትግበራን መምራት 
  • ከባለድርሻና አጋር አካላት ጋር በቅንጅት መስራት
  • የተለያዩ አገልግሎት አሰጣጥ ማሻሻያ ጥምረት ፎረሞችን መከታተልና መደገፍ 

  የሪፎርምና መልካም አስተዳደር  ዳይሬክቶሬት ኢኒሼቲቭስ 

  • የማህበረሰብ አስተያየት ምዘና ስርዓትን
  • የአመራር ተጠያቂነት ስርዓትን
  • የመልካም አስተዳደር ኢንዴክስ ምዘና