ቀጣይ የሙያ ግንባታ
In order for health workers to provide quality care and meet their communities’ changing health care needs, they must become lifelong learners dedicated to updating their professional knowledge, skil
In order for health workers to provide quality care and meet their communities’ changing health care needs, they must become lifelong learners dedicated to updating their professional knowledge, skil
ጤና ሚኒሰቴር ከኢትዮጵያ ጤና ትምህርትና ፕሮሞሽን ባለሙያዎች ማህበር እንዲሁም ከአጋር አካላት ጋር በመተባበር ሶስተኛውን ሃገር አቀፍ የማህበራዊ እና ባህሪ ለውጥ ጉባዔ “የማህበራዊ እና ባህሪ ለውጥ ተግባራት ለዘላቂ የጤና ልማት” በሚል መሪ ቃል ከ13 አለም አቀፍ አገራት ከመጡ የዘርፉ ባለሙያዎችን ጨምሮ 400 በላይ ተሳታፊዎች በተገኙበት በአዲስ አባባ በማካሄድ ላይ ይገኛል፡፡
ድጋፉ ሶስት ሚሊዮን የአሜሪካን ዶላር ወጪ የተደረገበት ሲሆን የቲቢ ፈጣን ሞለኪውላር ምርመራ በማድረግ የቲቢ በሽታን በፍጥነት ለማግኘት የሚያስችል ቴን ከለርድ የጂን ኤክስፐርት ማሽኖች ድጋፍ መሆኑ ታውቋል፡፡ በድጋፍ የተገኙት የጂን ኤክስፐርት ማሽኖቹ በተለይ ለተጎጂ ክልሎች እና የቲቢ ስርጭት ላለባቸው አካባቢዎች ላይ ላሉ ጤና ተቋማት እንደሚተላለፉ ተገልጿል።
የጤና ሚኒስትር ዴኤታ ዶክተር ደረጀ ድጉማ በድጋፉ የርክክብ ስነስርዓት ላይ እንደተናገሩት የጤና ሚኒስቴር የሳንባ ነቀርሳን ለማጥፋት አዲስ የ7 ዓመታት ስትራቴጂክ እቅድ ማዘጋጀቱንና ዩኤስኤአይዲ ኢትዮጵያ በአዲሱ ስትራቴጂክ ዕቅድ ውስጥ ቁልፍ ሚና እንደነበረው ጠቅሰው ለእቅዱ ስኬት መረጃን መሰረት ባደረገ፤ ውጤታማ በሆነ መንገድ መተግበርን ይጠይቃል ብሏል።
የጤና ሚኒስትር ዶክተር ሊያ ታደሠ በምርቃት ስነስርዓቱ ላይ ተገኝተው ባደረጉት ንግግር እንዳሉት የጤናው ዘርፍ በርካታ መሻሻሎች እያሣየ ያለ ቢሆንም ገና ብዙ ወደ ፊት መሄድ ይጠበቅበታል ብለዋል። የአክሶል ስትሮክ እና ስፓይን ማእከል መከፈቱ እንደ ሀገር የእስትሮክ ህክምናን አንድ ምእራፍ ወደ ፊት የሚወስድ መሆኑን ጠቅሰው ማእከሉ ለዚህ ምረቃ በመድረሱ ያላቸውን አድንናቆት ገልጸዋል። ይህ አዲስ ቴክኖሎጂ እና የተለየ አገልግሎት ይዞ የመጣ ማእከል በአገሪቱ መከፈት መቻሉ ለጤናው ዘርፍ ትልቅ አስተዋጽኦ እንደሚኖረውም ዶክተር ሊያ ተናግረዋል።
ላለፋት አመታት ተላላፊ ያልሆኑ በሽታዎች እና በዚህ ሳቢያ የሚመጣ ሞት እየጨመረ መምጣቱን የገለጹት ዶክተር ሊያ ይህን ችግር ለመቅረፍ የጤና ሚኒስቴር ከመከላከል ስራው ጎን ለጎን የስፔሻሊቲ ህክምና አገልገግሎት ማስፋፋት ስራ የሚያሰራ የአስር አመት ፍኖተ ካርታ ተዘጋጅቶ እየተተገበረ መሆኑን አስረድተዋል።
በዓለም አቀፍ ደረጃ በየዓመቱ በፈረንጆች ጥቅምት ወር የሚደረገው የጡት ካንሰር ግንዛቤ ማስጨበጫ ንቅናቄ በፓዮኒር ምርመራ ማዕከል ከመስከረም 20 ጀምሮ ለአንድ ወር በነፃና በግማሽ ክፍያ በሚሰጥ ምርመራ ተጀምሯል።
በየዓመቱ 40 ሺህ ያህል ሰዎች በጡት ካንሰር ምክንያት እንደሚሞቱ የጠቆሙት በጤና ሚኒስቴር የእናቶችና ሕፃናት ጤና ዳይሬክተር ዶክተር መሠረት ዘላለም ካንሰር ስር ከሰደደ በኋላ ለማከም የሚያደርሰውን የጤና፣ ማህበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ ጫና ለመቀነስና ለመከላከል ቀድሞ በመመርመር የጤናን ሁኔታ ማወቅ እንደሚገባ አሳስበዋል።
"በኑክሌር መስክ ዓለም አቀፍ ትብብር!" በሚል መሪ ቃል በቪየና ኦስትሪያ በተካሄደዉ 66ኛው የIAEA ጠቅላላ ጉባኤ ላይ በጤና ሚኒስትር ዴኤታ ክቡር ዶ/ር ደረጀ ዱጉማ የተመራ የኢትዮጵያ ልዑካን ቡድን ተሳትፈዋል፡፡
በኤጀንሲው ዋና መስሪያ ቤት በቪየና ኢንተርናሽናል ሴንተር (VIC) በቪየና ኦስትሪያ የተካሄደዉ ይህ ጉባኤ ከኒዩክሌር ቴክኖሎጂ እና ሳይንስ ዙሪያ ለህክምና አገልግሎት ጥቅም የሚዉሉ ቴክኖሎጂዎችን በተለይም የካንሰር ጨረር ህክምናን ጨምሮ ለተለያዩ ህክምና ዘርፎች ጥቅም ላይ በሚዉሉ የኑክሌር ቴክኖሎጂ እና ሳይንስ ርዕሰ ጉዳዮች ላይ መክረዋል፡፡
በ66ኛው የIAEA ጠቅላላ ጉባኤ የኢትዮጵያ ተወካዮች ከአክሽን ፎር ካንሰር ቴራፒ (PACT) መርሃ ግብሮች ቡድን ጋር በቀጥታ ውይይት በማድረግ በኢትዮጵያ እና በIAEA መካከል ስላለው እና የወደፊት የቴክኒክ ትብብር በተመለከተም ተወያይተዋል።
የጃፓን መንግስት በኢትዮጵያ የጤና አገልግሎትን ፍትሃዊና ተደራሽን ለማጠናከር የሚያግዙ የተሟላ የህክምና ቁሳቁስ ያላቸው 10 ተንቀሳቃሽ የህክምና ክሊኒኮችን ለመለገስ ከኢትዮጵያ መንግስት ጋር ስምምነት ተፈራርሟል
በጃፓን መንግስት በኩል ስምምነቱን የፈረሙት በኢትዮጵያ የጃፓን አምባሳደር ኢቶ ታኮኮ ባስተላለፉት መልዕክት በሀገራቸው የተደረገው የ500 ሚሊዮን የጃፓን የን/3.5 ሚሊዮን ዶላር/ ድጋፍ በኢትዮጵያ ከሚገኙ ክልሎች ድጋፍ የሚሹ ተብለው በተለዩት በአፋር፣ በሶማሌ፣ በቤንሻንጉል፣ በጋምቤላና በደቡብ ምዕራብ ክልሎች ያለውን የእናቶችና ህፃናት ጤና በማሻሻል የሚሞቱ እናቶችና ህፃናትን ቁጥር እንደሚቀንስ ያላቸውን ተስፋ ጠቁመው ተንቀሳቃሽ ክሊኒኮቹ አልትራሳውንድና ኤሌክትሮ ካርዲዮግራፍን ጨምሮ መሰረታዊ የህክምና ቁሳቁሶችን ያሟሉ እንደሚሆኑ ገልፀዋል፡፡
ጤና ሚኒስቴር በክረምቱ የበጎ ፈቃድ አገልገሎት ከቤት እድሳት በተጨማሪ የአረንጓዴ ልማትና የአካባቢ ጥበቃ፣ የትምህርት ቁሳቁሶች ድጋፍ፣ ነፃ የህክምና አገልግሎት፣ የደም ልገሳና ማዕድ ማጋራት ከአዲስ አበባ በተጨማሪ በሌሎችም ክልሎች ማከናወኑን የጤና ሚኒስቴር ሚኒስትር ዶ/ር ሊያ ታደሰን በመወከል አቶ እስክንድር ላቀው የንብረት አስተዳደርና ጠቅላላ አገልግሎት ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር ተናግረዋል።
በዘንድሮው ዓመት የክረምት በጎ ፍቃድ አገልግሎት ጤና ሚኒሰቴር ሰፋፊ ስራዎችን እየሰራ ሲሆን በተለይም ድጋፍ የሚሹ ቤተሰቦች ቤቶችን ከማደስ ጋር ተያይዞ ከአዲስ አበባ ከተማ በተጨማሪ በጋምቤላ ከተማም የአቅመ ደካማ ቤቶች እድሳት እያደረገ መሆኑን ተናግረዋል። በእለቱም ቤት ለታደሰላቸው አቅመ ደካማ ግለሰቦች የቁልፍ ርክክብ አድርገዋል።
በሰቆጣ ቃልኪዳን የተገኙ መልካም ተሞክሮዎችን ለሌሎች የአፍሪካ ሃገራት በማጋራት በአፍሪካ ደረጃ መቀንጨርን ለማስቀረት፣ የሰው ሀብትን ለማሳደግ፣ እና በዘርፉ እድገትን ለማፋጠን አላማ አድርጎ በኢትዮጵያ መንግስት እና በአፍሪካ ልማት ባንክ ትብብር የተባበሩት መንግስታት አጠቃላይ ጉባኤ እየተካሄደ ባለበት በአሜርካ ኒዉዮርክ ከተማ የተዘጋጀ የጎንዮሽ መድረክ ነው።
በመድረኩ ላይ ኢትዮጵያ የመቀንጨር ምጣኔን ከመቀነስ አኳያ እየሰራች ያለውን ዘርፍ ብዙ ትብብርና ምላሽ አጠቃላይ ልምድና በሰቆጣ ቃልኪዳን ስምምነት የተገኙ መልካም ተሞክሮ በኢፌድሪ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር በክቡር አቶ ደመቀ መኮንን ቀርበዋል።
ኮንፍረንሱ የተካሄደው በኢትዮጵያ የሚታየውን የመድሃኒት አቅርቦት ውስንንት ለመሙላት እንዲቻል መድሃኒት አምራች እና አቅራቢዎችን ለመሳብ ታስቦ መሆኑን የኢትዮጵያ መድሃኒት አቅራቢዎች አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር አብዱልካዲር ገልገሎ ገልጸዋል፡፡
ዶ/ር አብዱልካዲር በንግግራቸው እንዳወሱት መድሃኒት አቅርቦት የባለድርሻ አካላት እና የካፒታል ስብጥር የሚጠይቅ በመሆኑ ከአቅራቢዎች ጋር ስትራተጂክ ፓርትነርሺፕ ግንኙነትን ማጠናከር እንደሚያስፈልግ ተናግረዋል።
መድሃኒት አቅርቦት በአለም አቀፍ ደረጃ ትኩረት የተሰጠው መሆኑን የተናገሩት የኢትዮጵያ ምግብ እና መድሃኒት ኤጀንሲ ዳይሬክተር ሄራን ገርባ ሲሆኑ፤ ኮቪድ 19 የመድሃኒት አቅርቦት ሰንሰለት ላይ ችግር መፍጠሩን ተናግረው ኤጀንሲያቸው የመድሃኒት ጥራት ቁጥጥር እና ደህንነት ላይ ትኩረት በማድረግ እየሰራ መሆኑን እና አገልግሎቱን ለማሻሻል የዲጂታላይዜሽን ስራ በመስራት ላይ መሆኑን ዳይሬክተሯ ተናግረዋል፡፡