በጤና ሚኒስትር ክብርት ዶ/ር ሊያ ታደሰ የሚመራ የኢትዮጵያ ልዑካን ቡድን በ75 ኛው የአለም ጤና ጉባኤ ላይ እየተሳተፈ ነው።

  • Time to read less than 1 minute
World Health Assembly

የኮቪድ 19 ወረርሽኝ ከተከሰተ ወዲህ በአካል የመጀመሪያ የሆነው ይህ የጤና ጉባኤ ግንቦት 14, 2014 ዓ.ም  በጄኔቫ ዝዊዘርላንድ በይፋ ተጀምሯል። 


"ሰላም ለጤና ጤና ለሰላም!"( "Peace for Health and Health for peace!") በሚል መሪ ቃል እየተካሄደ ያለው 75 ኛው የአለም ጤና ጉባኤ ላይ የአለማችን የማህበረሰብ ጤና  አሁናዊና ቀጣይ  ስትራቴጅክ ጉዳዮች ቀርበው ምክክርና ውይይት የሚደረግ ሲሆን ጉባኤው ለአንድ ሳምንት በጄኔቫ የሚቀጥል ይሆናል።