በጤና ሚኒስቴር እና ግብርና ሚኒስቴር የሚመራ የዓለም ጤና ድርጅት የምግብና የእርሻ ድርጅትን እንዲሁም ዩኒሴፍን ያካተተው ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች ቡድን በዛሬው እለት በኦሮሚያ ክልል በድርቅ የተጎዳዉን የቦረና ዞንን ጎብኝቷል። 

  • Time to read less than 1 minute
Borena

በዱቡሉቅ ወረዳ የዱቡሉቅ ጤና ጣቢያ አጣዳፊ የምግብ እጥረት ህክምና መስጫ ማዕከልንና የመጠጥ ውሃ ጥራት ቁጥጥርን እንዲሁም በድርቁ የተጎዱ የማህበረሰብ ክፍሎችን ቡድኑ ተመልክቷል። 


በጉብኝቱም ቡድኑ ከዞኑ አመራሮች ጋር በወቅታዊዉ ሁኔታና የድንገተኛ ድጋፍ አሰጣጥን አስመልክቶ ውይይት ያደረገ ሲሆን በድርቁ የተጎዱ እና የጤና እና የምግብ እጥረት ጉዳት የደረሰባቸዉን ዜጎች ለማከም፤ ለመደገፍ የሚዉሉ ከአለም ጤና ድርጅት የተገኙ 31 ሜትሪክ ቶን የድንገተኛ ህክምና ቁሳቁስ ድጋፎችንም አበርክቷል።


በቀጣይም ክፍተት ባለባቸው ላይ የፌደራል መንግስትና አጋር አካላትና ድጋፉን አጠናክረው እንደሚቀጥሉ ገልጸዋል።