ቀጣይ የሙያ ግንባታ
In order for health workers to provide quality care and meet their communities’ changing health care needs, they must become lifelong learners dedicated to updating their professional knowledge, skil
In order for health workers to provide quality care and meet their communities’ changing health care needs, they must become lifelong learners dedicated to updating their professional knowledge, skil
የጤና ሚኒስቴር መተግበሪያውን ወደ ስራ ለማስገባት ከማስተር ካርድ፣ ከጋቪ እና ከጄ ኤስ አይ ጋር ዛሬ ስምምነት ተፈራርሟል።
የጤና ሚኒስትር ዶክተር ሊያ ታደሰ በፊርማ ስነ ስርዓቱ ላይ በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ ላይ እንደተናገሩት ሚኒስቴር መስርያ ቤቱ በሁለተኛው የጤናው ዘርፍ እቅድ ውስጥ በመረጃ ላይ የተመሰረተ የውሳኔ አሰጣጥ ስርዓት ለማጠናከር ጥራት ያለው መረጃ ማሰባሰብ፣ መተንተን እና መጠቀም ቁልፍ ተግባራት አድርጎ በልዩ ትኩረት እየተሰራ እንደሚገኝ ገልጸው በዚሁ ወቅት ዲጅታል መተግበሪያው በሙከራ ደረጃ መጀመሩ በጤናው ዘርፍ ያለውን የመረጃ ስርዓት ለማዘመን እንደሚረዳ ገልፀዋል።
የታካሚዎችን የጤና መረጃ ስርዓት ፍሰትን ለማቀላጠፍ ማስተር ካርድ ‹‹ዌልነስ ፓስ›› የተባለው የዲጅታል መላ የሙከራ ትግበራውም በተመረጡ የጤና ተቋማት በ15 ወራት ውስጥ ለአንድ ሚሊዮን ተገልጋዮች ለማዳረስ የታለመ መሆኑን አስታውቀዋል፡፡
የ100 የልብ ህሙማን ህጻናት ህክምናና የአየር ቲኬት ሙሉ ወጪ በመሸፈን ህንድ ሃገር ለማሳከም የመግባቢያ ሰነድ በጤና ሚኒስቴር፣ በኢትጵያ አየር መንገድ፣ በሮታሪ ኢንተርናሽናል እና በኢትጵያ ልብ ህሙማን ማህበር የተፈረመ ሲሆን፣ በኢትዮጵያ የሚከሰቱ ተላላፊ ያልሆኑ በሽታዎችን ለመከላከል የሚሰራውን ስራ የሚያጠናክር የመግባቢያ ሰነድ መሆኑን የጤና ሚኒስቴር ዶ/ር ሊያ ታደሰ አስታውቀዋል፡፡
በመንግስት ተቋማትና በኢትዮጵያ የልብ ህሙማን ህጻናት መርጃ ማእከል ብቻ ከ7,000 በላይ ህጻናት ለልብ ቀዶ ህክምና ወረፋ እየጠበቁ እንደሚገኙ የተናገሩት ዶ/ር ሊያ፤ እነዚህን ችግሮች ታሳቢ ባደረገ መልኩ ዛሬ ሁለት የመግባቢያ ሰነዱች እንደተፈረሙ ገልጸዋል፡፡
የጤና ሚኒስትር ዶ/ር ሊያ ታደሰ በስዊዘርላንድ ጀኔቫ "ሰላም ለጤና ጤና ለሰላም!” በሚል መሪ ቃል እየተካሄደ ባለው 75ኛው አመታዊ የአለም ጤና ጉባኤ ላይ እንደተናገሩት ጤንነቱ የተጠበቀ ማህበረሰብን መፍጠር መቻል አስተማማኝና ዘለቄታዊ ያለው ሰላም እንዲኖር ከማድረግ አንጻር ያላው ድርሻ ከፍተኛ መሆኑን ተናግረዋል።
ያለሰላም የተሟላ ጤናም መኖር አይችልም ያሉት ሚኒስትሯ በሰሜን ኢትዮጵያ በተከሰተው ግጭት በርካታ የጤና ተቋማት እንደወደሙና እንደተዘረፉ በዚህም በርካታ ቁጥር ያለው ህብረተሰብ የተሟላ የጤና አገልግሎት እንዳያገኝ መስተጓጓሉን ጠቅሰው የኢትዮጵያ መንግስት ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በመሆን የጤና አገልግሎትን ወደነበረበት ለመመለስ ከፍተኛ ጥረት እያደረገ መሆኑን ገልጸዋል።
የኮቪድ 19 ወረርሽኝ ከተከሰተ ወዲህ በአካል የመጀመሪያ የሆነው ይህ የጤና ጉባኤ ግንቦት 14, 2014 ዓ.ም በጄኔቫ ዝዊዘርላንድ በይፋ ተጀምሯል።
"ሰላም ለጤና ጤና ለሰላም!"( "Peace for Health and Health for peace!") በሚል መሪ ቃል እየተካሄደ ያለው 75 ኛው የአለም ጤና ጉባኤ ላይ የአለማችን የማህበረሰብ ጤና አሁናዊና ቀጣይ ስትራቴጅክ ጉዳዮች ቀርበው ምክክርና ውይይት የሚደረግ ሲሆን ጉባኤው ለአንድ ሳምንት በጄኔቫ የሚቀጥል ይሆናል።
በመድረኩ በዓለም መንግስታት የሚደገፍ መንግስታዊ እና መንግስታዊ ያልሆኑ ሲቪክ ማህበራት፣ የተባበሩት መንግስታት ኤጀንሲዎች፣ የልማት ባንኮች እና ሌሎች ባለድርሻ አካላት የተገኙ ሲሆን ውይይቱ በዘላቂ የልማት ግብ 6 ማለትም ዘላቂ የመሰረታዊ ውሃ፣ ሳኒቴሽን እና ሀይጅን አገሌግሎት ለሁሉም ማዳረስ ላይ ያጠነጠነ ነው።
በጃካርታ እየተካሄደ ያለው መድረክ በዋነኝነት በ2030 እ.ኤ.አ የውሃ፣ ሳኒቴሽን እና ሀይጅን አገልግሎቶችን ግብ ለማሳካት ወሳኝ በሆኑት የፖለቲካ ቁርጠኝነት፣ተጨማሪ ኢንቨስትመንት፣ አመራር እና ተጠያቂነት ላይ ትኩረት ያደረገ ነው ተብሏል።
በሁለት ቀናት ቆይታው ከውሃ፣ ከሳኒቴሽን እና ከሃይጅን ርዕሰ ጉዳዮች በተጨማሪ የጎንዮሽ ውይይቶች በዘርፉ ሚኒስትሮች ይደረጋሉ ተብሎ ይጠበቃል፡፡
በቅርቡ የታተመው የላንሴት ግሎባል የጤና ኮሚሽን ሪፖርት ላይ በማተኮር "የህብረተሰብ ጤና ክብካቤ ላይ መዋዕለ ንዋይ በማፍሰስ ሰውን ማስቀደም" በሚል መሪ ቃል የጤና ሚኒስቴር ሚኒስትር ዶክተር ሊያ ታደሰ በተገኙበት የመጀመሪያ ደረጃ የጤና ክብካቤ ፋይናንስ ላይ ትኩረቱን ያደረገ መድረክ የክልል ጤና ቢሮ ኃላፊዎች የጤና ሚኒስቴር ተጠሪ ተቋማት እንዲሁም የገንዘብ ሚኒስቴር እና አጋር ድርጅቶችን በማካተት አውደ ጥናት አካሄዷል፡፡
በአገራችን በሽታን በመካከልና ጤና ማበልጸግ ፖሊሲን በመቅረጽ የመጀመሪያ ደረጃ የጤና አጠባበቅ ዘዴን ተግባራዊ እየተደረገ እንደሚገኝና የጤና ኤክስቴንሽን መርሃ ግብር ማሻሻያ ፍኖተ ካርታንም በመዘርጋት ሞዴል ወረዳዎችን ለመፍጠር፣ የማህበረሰብ አቀፍ የጤና መድህን ሸፋንን ለማሳደግ እና ሁሉንም የጤና ተቋማት ወደ ከፍተኛ አፈጻጸም ለመቀየር በመላ ሀገሪቱ እየተሰራበት እንደሚገኝ ሚኒስትር ዶ/ር ሊያ ተደሰ በመድረኩ ላይ ተናግረዋል፡፡
የጤና ሚኒስቴር ከደብረብርሀን ዩንቨርሲቲ፣ ከስማይል ትሬን (Smile Train) እና ከኬፕ ታውን ዩንቨርሲቲና ጋር በመቀናጀት ለ3 ቀናት በአዲስ አበባ ሲያካሂድ የነበረውን የዓለም የቀዶ ህክምና፣ የድገተኛና ፅኑ ህሙማን ህክምና አገልግሎት የአመራር ክህሎት ዓውደ ርዕይ ተጠናቋል፡፡
በጥናታዊ ዓውደ ርዕዩ የማጠቃለያ መርሐ ግብሩ ላይ የተገኙት የጤና ሚንስቴር ሚንስትር ዲኤታ ዶ/ር አየለ ተሾመ እንደተናገሩት አውደ ርዕዩ በዓለም አቀፍ የቀዶ ሕክምናና የድንገተኛና ጸኑ ህክምና ላይ ትኩረት አድርጎ መወያየቱ የሚደገፍና ትክክለኛው ጊዜ መሆኑን ጠቅሰው እንደ ሃገር የአገልግሎቱን ጥራትና ተደራሽነት ለማስፋፋት የጤና ሚኒስቴር በ5 ዓመቱ እስራቴጂክ ዕቅድ አካቶ በትኩረት እየሰራ መሆኑን አስታውቀዋል፡፡
የሀገራችን የጤና ስርዓትን በማጠናከር የሀገር ውስጥና ድንበር ተሻጋሪ የጤና በሽታዎችን ለመከላከልና ለመቆጣጠር የበለጠ ተግቶ መስራት እንዲቻል በዛሬው እለት በኢትዮጵያ የሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት በአውሮፓ ህብረት ድጋፍና በምስራቅ አፍሪካ በየነ-መንግስታት ድርጅት (ኢጋድ)እንዲሁም በዩኖፕስ አስተባባሪነት የኢትዮጵያንና የአጎራባች ሀገራት የጤና ስርዓትና የኮቪድ-19 ምላሽን ለመደገፍ ለኢትዮጵያ የጤና ሚኒስቴር በተደረገው ልዩ ልዩ የጤና አምቡላንሶችና ቁሳቁሶች ርክክብ እና የመግባቢያ ሠነድ ፊርማ ሥነ-ሥርዓት ላይ የጤና ሚኒስትር ክብርት ዶ/ር ሊያ ታደሰ እንደገለጹት የተሻለ ጤናን መኖር የሚቻለው የተሻለ የጤና ሥርዓት ሲገነባ እንደሆነ በአጽንኦት ተናግረዋል፡፡
በጤና ኤክስቴንሽን መርሃ-ግብር ትግበራ በርካታ የጤና አገልግሎቶች ማህበረሰቡን ተደራሸ ለማድረግ የአጋር ድርጅቶች ሚና ውጤታማ እንደነበር እና እንደ ሃገር አመርቂ የጤና ውጤቶች የተመዘገበበት እንደሆነ ተጠቁሟል፡፡
በፕሮግራሙ ላይ ተገኝተው ንግግር ያደረጉት የጤና ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴኤታ ዶ/ር ደረጄ ድጉማ እንደገለጹት የጤና ስርዓታችን በተለይም የእናቶችና ህጻናት ጤና አገልግሎትና የመጀመሪያ ደረጃ የጤና አገልግሎት ተጠቃሚ የሆነበት የጄ ኤስ አይ/ኤል10ኬ 10 ኪሎ ሜትር/JSI L10K 10K/ ባለፉት 14 ዓመታት የነበረው አገልግሎት ውጤታማ እንደነበር አንስተው ከጤና ሚኒስቴር ጋር በቅንጅት በመስራት ለተገኘው ውጤትና ድጋፍ ላደረጉ አካላት ምስጋናቸውን አቅርበው። በቀጣይም ይህ ፕሮጅክት ቀጣይነት እንዲኖረው ድጋፍ የሚያደርጉ አካላት በትብብር ውጤታማ ስራ ለመስራት ድጋፋቸውን አጠናክረው እንዲቀጥሉ ጥሪያቸውን አስተላልፈዋል፡፡