የብቃት ምዘና ፈተና ለምትወስዱ ጤና ባለሙያዎች በሙሉ
የጤና ሚኒስቴር ከከፍተኛ የትምህርት ተቋማት በሜዲስን፤ ነርሲንግ፤ ጤና መኮንን፤ አንስቴዥያ፤ ፋርማሲ ፤ሜዲካል ላቦራቶሪ፤ ሚድዋይፈሪ፤ ዴንታል ሜዲስን፤ ሜዲካል ራዲዮሎጂ፤ ኢንቫይሮመንታል ሄልዝ፤ ፔዲያትሪክ ኤንድ ቻይልድ ሄልዝ፤ ሳይካትሪ ነርሲንግ፤ እና ኢመርጀንሲ ኤንድ ክሪቲካል ኬር ነርሲንግ ሙያዎች በመጀመሪያ ዲግሪ ተመርቀው የብቃት ምዘና ፈተና ለመውሰድ በመጠባበቅ ላይ ለሚገኙ የጤና ባለሙያዎች ፈተናው ከግንቦት 14- 18/ 2015 ዓ.ም የሚሰጥ መሆኑን እየገለፅን :-
- የፈተናው አሰጣጥ ሂደት በኮምፒውተር ይሆናል።
- የፈተናው መርሃግብር
- - 14/9/2015 ዓ.ም…………………………………Nursing
- - 16/9/2015 ዓ.ም…………………………………Pharmacy, Public Health, Anesthesia, Medical Radiology Technology and Environmental Health
- - 18/9/2015 ዓ.ም………………………………..Medical Laboratory Science, Midwifery, Medicine, Dental Medicine, Pediatric and Child Health Nursing, Psychiatric Nursing and Emergency and Critical Care Nursing
- እያንዳንዱ ተፈታኝ ከሚፈተንበት ቀን አንድ ቀን ቀደም ብሎ ማለትም ግንቦት 13፣15 እና 17/2015 ዓ.ም ከጠዋቱ በ 3፡00 ሰዓት በመፈተኛ ጣቢያ በመገኘት ስለፈተናው አሰጣጥ ቅድመ ገለጻ (orientation) መከታተል፤ የቅድመ ፈተና መለማመጃ ጥያቄዎችን መስራትና፤ የመፈተኛ ክፍሉን መለየት ይኖርበታል:: በፈተና ገለፃው (orientation) ላይ ያልተገኘ ተመዛኝ ፈተናውን መውሰድ የማይችል መሆኑን በጥብቅ እናሳስባለን።
- በፈተናው ዕለት ማንነታችሁን የሚገልጽ መታወቂያ (የቀበሌ መታወቂያ፣ ፓስፖርት፣ መንጃ ፍቃድ ወይም ሌላ በግልጽ የሚታይ ህጋዊ መታወቂያ)፣ የፈተና መስሪያ ግብዓቶች (እስኪሪብቶ ብቻ) ይዛችሁ መገኘት ይኖርባችኋል፡፡
- ከላይ ከተጠቀሱት ነገሮች ውጪ ምንም አይነት የኤሌክትሮኒክስ መሳሪያ (ስልክ፣ የእጅ ሰዓት፣ መነጽር (የተረጋገጠ የዕይታ ችግር ከሌለ በስተቀር)፣ ቦርሳ እና ሌሎች እቃዎች፣ ምንም አይነት ማጣቀሻዎች እንዲሁም ባዶ ወረቀቶች፣ ምግብ ወይም መጠጥ (የተረጋገጠ የጤና ችግር ከሌለ በስተቀር) ይዞ መግባት አይፈቀድም፡፡
- በፈተናው ወቅት ተመዛኞች በሁለቱም ክፍለ ጊዜ (ጠዋት እና ከሰዓት በኋላ) አቴንዳንስ ላይ በአግባቡ መፈረማችሁን ማረጋገጥ ይኖርባችኋዋል፣
- ማንኛውም ተመዛኝ ወደ ፈተና ጣቢያ ሲመጣ ሲስተሙ የሚሰጠውን የፈተና መለያ ቁጥር (Registration No) QR code የያዘ ወረቀት /ስሊፕ/ print አድርጎ ካልያዘ ፈተናውን መውሰድ የማይችል መሆኑን በጥብቅ እናሳስባለን፡፡
- ተመዛኞች ወደ ጣቢያ ከመምጣታችሁ በፊት ከዚህ ማስታወቂያ ጋር የተያያዘውን ማስወንጨፊያ በመጫን የመረጣችሁትን የፈተና ጣቢያዎች መመልከት ይኖርባችኋል።
- የመፈተኛ ጣቢያ ኦንላይን በመረጣችሁት መሰረት ስም ዝርዝራችሁን ከዚህ በታች ያለውን ማስወንጨፊያ በመጫን መመልከት ይኖርባችኋል፡፡
- Adama Science and Technology,
- Addis Ababa Science and Technology university,
- Addis Ababa University(5 kilo),
- Addis Ababa University (Black Lion),
- Ambo university(Main Campus),
- Ambo University (Hacalu Campus),
- Arba Minch University,
- Bahir Dar University (Peda Campus),
- Debre Birhan University (Asrat Weldeyes Campus),
- Haremaya University(Main Campus),
- Hawassa University(Main Campus),
- Jigjiga University (Main Campus),
- Jimma University (Techno Campus),
- Mekele University (Ayder Referral Hospital),
- St. Paul Hospital Millinium Medical Collage,
- University of Gonder (HSC),
- University of Gonder (Tewodros Campus),
- Wachamo University,
- Wolayta Sodo University (Main Campus),
- Wolkite University,
- Wollo University (Kombolcha Campus)
- ተመዛኞች ስማቸው ከተጠቀሰበት ተቋም ውጪ በፍጹም ፈተናውን መውሰድ የማትችሉ መሆኑን እናሳስባለን፡፡
- በኮምፒውተር የታገዘ ፈተና ላይ የተሻለ ግንዛቤ እንዲኖራችሁ ከስር ያለውን አጭር ቪዲዩ ተከታተሉ። ለተጨማሪ መረጃ በስልክ ቁጥር 0118275936/952 መደወል ይቻላል፡፡