በጤና ሚኒስቴር የተጀመረው በምሳ ሰአት እንማማር ፕሮግራም ዛሬ ለሁለተኛ ጊዜ ተካሄዷል፡፡ የሚኒስቴር መስሪያቤቱ አመራሮች በየሳምንቱ በምሳ ሰአት የሚያካሂዱት የመማማሪያ መድረክ ዛሬም ቀጥሎ የተካሄደ ሲሆን በዛሬው መርሀግብር የቡድን ግንባታ(ቲም ቢውልዲንግ ) የመማማሪያው ርእሰ ጉዳይ ነበር፡፡ሚኒስትር ዴኤታዋ ዶክተር ሊያ ታደሰ ስራዎችን በቅንጅት እና አንድ መንፈስ ለማከናወን የሚያስችለው የቡድን ስራ መሆኑን ገልጸው ብድን እንዴት እንደሚገነባ መወያያ ሰነድ አቅርበዋል፡፡ የአመራር አባላቱም ውይይት አድርገውበታል ፡፡